Surah At-Takathur - Amharic Translation by Muhammed Sadiq And Muhammed Sani Habib
أَلۡهَىٰكُمُ ٱلتَّكَاثُرُ
በብዛት መፎካከር (ጌታችሁን ከመገዛት) አዘነጋችሁ፡፡
Surah At-Takathur, Verse 1
حَتَّىٰ زُرۡتُمُ ٱلۡمَقَابِرَ
መቃብሮችን እስከ ጎበኛችሁ ድረስ፡፡
Surah At-Takathur, Verse 2
كَلَّا سَوۡفَ تَعۡلَمُونَ
ተከልከሉ፤ ወደፊት (ውጤቱን) ታውቃላችሁ፡፡
Surah At-Takathur, Verse 3
ثُمَّ كَلَّا سَوۡفَ تَعۡلَمُونَ
ከዚያም ተከልከሉ፤ ወደ ፊት ታውቃላችሁ፡፡
Surah At-Takathur, Verse 4
كَلَّا لَوۡ تَعۡلَمُونَ عِلۡمَ ٱلۡيَقِينِ
በእውነቱ (የሚጠብቃችሁን) እርግጠኛ ዕውቀትን ብታውቁ ኖሮ፤ (ባልዘናጋችሁ ነበር)፡፡
Surah At-Takathur, Verse 5
لَتَرَوُنَّ ٱلۡجَحِيمَ
ገሀነምን በእርግጥ ታያላችሁ፡፡
Surah At-Takathur, Verse 6
ثُمَّ لَتَرَوُنَّهَا عَيۡنَ ٱلۡيَقِينِ
ከዚያም እርግጠኛን ማየት ታዩዋታላችሁ፡፡
Surah At-Takathur, Verse 7
ثُمَّ لَتُسۡـَٔلُنَّ يَوۡمَئِذٍ عَنِ ٱلنَّعِيمِ
ከዚያም ከድሎታችሁ ሁሉ በዚያ ቀን ትጠየቃላችሁ፡፡
Surah At-Takathur, Verse 8