Surah Al-Qaria - Amharic Translation by Muhammed Sadiq And Muhammed Sani Habib
ٱلۡقَارِعَةُ
ቆርቋሪይቱ (ጩኸት)፤
Surah Al-Qaria, Verse 1
مَا ٱلۡقَارِعَةُ
ምን አስደናቂ ቆርቋሪ ናት
Surah Al-Qaria, Verse 2
وَمَآ أَدۡرَىٰكَ مَا ٱلۡقَارِعَةُ
ቆርቋሪይቱም ምን እንደኾነች ምን አሳወቀህ
Surah Al-Qaria, Verse 3
يَوۡمَ يَكُونُ ٱلنَّاسُ كَٱلۡفَرَاشِ ٱلۡمَبۡثُوثِ
ሰዎች እንደ ተበታተነ ቢራቢሮ (ወይም ኩብኩባ) በሚኾኑበት ቀን፤
Surah Al-Qaria, Verse 4
وَتَكُونُ ٱلۡجِبَالُ كَٱلۡعِهۡنِ ٱلۡمَنفُوشِ
ጋራዎችም እንደ ተነደፈ ሱፍ በሚኾኑበት (ቀን ልቦችን በድንጋጤ ትቆረቁራለች፡፡)
Surah Al-Qaria, Verse 5
فَأَمَّا مَن ثَقُلَتۡ مَوَٰزِينُهُۥ
ሚዛኖቹ የከበዱለት ሰውማ፤
Surah Al-Qaria, Verse 6
فَهُوَ فِي عِيشَةٖ رَّاضِيَةٖ
እርሱ በምትወደድ ኑሮ ውስጥ ይኾናል፡፡
Surah Al-Qaria, Verse 7
وَأَمَّا مَنۡ خَفَّتۡ مَوَٰزِينُهُۥ
ሚዛኖቹም የቀለሉበት ሰውማ፤
Surah Al-Qaria, Verse 8
فَأُمُّهُۥ هَاوِيَةٞ
መኖሪያው ሃዊያህ ናት
Surah Al-Qaria, Verse 9
وَمَآ أَدۡرَىٰكَ مَا هِيَهۡ
እርሷም ምን እንደ ኾነች ምን አሳወቀህ
Surah Al-Qaria, Verse 10
نَارٌ حَامِيَةُۢ
(እርሷ) በጣም ተኳሳ እሳት ናት፡፡
Surah Al-Qaria, Verse 11