Surah Al-Maun - Amharic Translation by Muhammed Sadiq And Muhammed Sani Habib
أَرَءَيۡتَ ٱلَّذِي يُكَذِّبُ بِٱلدِّينِ
ያንን በምርመራው የሚያስተባብለውን አየህን? (ዐወቅከውን)
Surah Al-Maun, Verse 1
فَذَٰلِكَ ٱلَّذِي يَدُعُّ ٱلۡيَتِيمَ
ይህም ያ የቲምን በኀይል የሚገፈትረው፤
Surah Al-Maun, Verse 2
وَلَا يَحُضُّ عَلَىٰ طَعَامِ ٱلۡمِسۡكِينِ
ድኻንም በማብላት ላይ የማያግባባው ሰው ነው፡፡
Surah Al-Maun, Verse 3
فَوَيۡلٞ لِّلۡمُصَلِّينَ
ወዮላቸው ለሰጋጆች፡፡
Surah Al-Maun, Verse 4
ٱلَّذِينَ هُمۡ عَن صَلَاتِهِمۡ سَاهُونَ
ለእነዚያ እነርሱ ከስግደታቸው ዘንጊዎች ለኾኑት፤ (ሰጋጆች)፡፡
Surah Al-Maun, Verse 5
ٱلَّذِينَ هُمۡ يُرَآءُونَ
ለእነዚያ እነርሱ ይዩልኝ ባዮች ለኾኑት፡፡
Surah Al-Maun, Verse 6
وَيَمۡنَعُونَ ٱلۡمَاعُونَ
የዕቃ ትውስትንም (ሰዎችን) የሚከለክሉ ለኾኑት (ወዮላቸው)፡፡
Surah Al-Maun, Verse 7