UAE Prayer Times

  • Dubai
  • Abu Dhabi
  • Sharjah
  • Ajman
  • Fujairah
  • Umm Al Quwain
  • Ras Al Khaimah
  • Quran Translations

Surah Ar-Rahman - Amharic Translation by Muhammed Sadiq And Muhammed Sani Habib


ٱلرَّحۡمَٰنُ

አል-ረሕማን፤
Surah Ar-Rahman, Verse 1


عَلَّمَ ٱلۡقُرۡءَانَ

ቁርኣንን አስተማረ፡፡
Surah Ar-Rahman, Verse 2


خَلَقَ ٱلۡإِنسَٰنَ

ሰውን ፈጠረ፡፡
Surah Ar-Rahman, Verse 3


عَلَّمَهُ ٱلۡبَيَانَ

መናገርን አስተማረው፡፡
Surah Ar-Rahman, Verse 4


ٱلشَّمۡسُ وَٱلۡقَمَرُ بِحُسۡبَانٖ

ፀሐይና ጨረቃ በተወሰነ ልክ (ይኼዳሉ)፡፡
Surah Ar-Rahman, Verse 5


وَٱلنَّجۡمُ وَٱلشَّجَرُ يَسۡجُدَانِ

ሐረግና ዛፍም (ለእርሱ) ይሰግዳሉ፡፡
Surah Ar-Rahman, Verse 6


وَٱلسَّمَآءَ رَفَعَهَا وَوَضَعَ ٱلۡمِيزَانَ

ሰማይንም አጓናት፡፡ ትክክለኛነትንም ደነገገ፡፡
Surah Ar-Rahman, Verse 7


أَلَّا تَطۡغَوۡاْ فِي ٱلۡمِيزَانِ

በሚዛን (ስትመዝኑ) እንዳትበድሉ፡፡
Surah Ar-Rahman, Verse 8


وَأَقِيمُواْ ٱلۡوَزۡنَ بِٱلۡقِسۡطِ وَلَا تُخۡسِرُواْ ٱلۡمِيزَانَ

መመዘንንም በትክክል መዝኑ፡፡ ተመዛኙንም አታጉድሉ፡፡
Surah Ar-Rahman, Verse 9


وَٱلۡأَرۡضَ وَضَعَهَا لِلۡأَنَامِ

ምድርንም ለፍጡሩ አደላደላት፡፡
Surah Ar-Rahman, Verse 10


فِيهَا فَٰكِهَةٞ وَٱلنَّخۡلُ ذَاتُ ٱلۡأَكۡمَامِ

በውስጧ እሸት ባለ ሺፋኖች የኾኑ ዘንባባዎችም ያሉባት ስትኾን፡፡
Surah Ar-Rahman, Verse 11


وَٱلۡحَبُّ ذُو ٱلۡعَصۡفِ وَٱلرَّيۡحَانُ

የገለባ ባለቤት የኾነ ቅንጣትም፡፡ ባለ መልካም መዐዛ ቅጠሎችም (ያሉባት ስትኾን)፡፡
Surah Ar-Rahman, Verse 12


فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ

(ሰዎችና ጋኔኖች ሆይ!) ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ
Surah Ar-Rahman, Verse 13


خَلَقَ ٱلۡإِنسَٰنَ مِن صَلۡصَٰلٖ كَٱلۡفَخَّارِ

ሰውን እንደ ሸክላ ከሚቅጨለጨል ደረቅ ጭቃ ፈጠረው፡፡
Surah Ar-Rahman, Verse 14


وَخَلَقَ ٱلۡجَآنَّ مِن مَّارِجٖ مِّن نَّارٖ

ጃንንም ከእሳት ከኾነ ነበልባል ፈጠረው፡፡
Surah Ar-Rahman, Verse 15


فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ
Surah Ar-Rahman, Verse 16


رَبُّ ٱلۡمَشۡرِقَيۡنِ وَرَبُّ ٱلۡمَغۡرِبَيۡنِ

የሁለቱ ምሥራቆች ጌታ፤ የሁለቱ ምዕራቦችም ጌታ ነው፡፡
Surah Ar-Rahman, Verse 17


فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ
Surah Ar-Rahman, Verse 18


مَرَجَ ٱلۡبَحۡرَيۡنِ يَلۡتَقِيَانِ

ሁለቱን ባሕሮች የሚገናኙ ሲኾኑ ለቀቃቸው፡፡
Surah Ar-Rahman, Verse 19


بَيۡنَهُمَا بَرۡزَخٞ لَّا يَبۡغِيَانِ

(እንዳይዋሐዱ) በመካከላቸው ጋራጅ አልለ፡፡ (አንዱ ባንዱ ላይ) ወሰን አያልፉም፡፡
Surah Ar-Rahman, Verse 20


فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታሰተባብላላችሁ?›
Surah Ar-Rahman, Verse 21


يَخۡرُجُ مِنۡهُمَا ٱللُّؤۡلُؤُ وَٱلۡمَرۡجَانُ

ሉልና መርጃን ከሁለቱ ይወጣል፡፡
Surah Ar-Rahman, Verse 22


فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ
Surah Ar-Rahman, Verse 23


وَلَهُ ٱلۡجَوَارِ ٱلۡمُنشَـَٔاتُ فِي ٱلۡبَحۡرِ كَٱلۡأَعۡلَٰمِ

እንደ ጋራዎች ኾነው በባሕር ውስጥ የተሠሩት ተንሻለዮቹም (ታንኳዎች) የእርሱ ናቸው፡፡
Surah Ar-Rahman, Verse 24


فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ
Surah Ar-Rahman, Verse 25


كُلُّ مَنۡ عَلَيۡهَا فَانٖ

በእርሷ (በምድር) ላይ ያለው ሁሉ ጠፊ ነው፡፡
Surah Ar-Rahman, Verse 26


وَيَبۡقَىٰ وَجۡهُ رَبِّكَ ذُو ٱلۡجَلَٰلِ وَٱلۡإِكۡرَامِ

የልቅናና የልግሥና ባለቤት የኾነው የጌታህ ፊትም ይቀራል፡፡ (አይጠፋም)፡፡
Surah Ar-Rahman, Verse 27


فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ
Surah Ar-Rahman, Verse 28


يَسۡـَٔلُهُۥ مَن فِي ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلۡأَرۡضِۚ كُلَّ يَوۡمٍ هُوَ فِي شَأۡنٖ

በሰማያትና በምድር ውስጥ ያሉት ሁሉ ይለምኑታል፡፡ በየቀኑ ሁሉ እርሱ በሥራ ላይ ነው፡፡
Surah Ar-Rahman, Verse 29


فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታሰተባብላላችሁ?›
Surah Ar-Rahman, Verse 30


سَنَفۡرُغُ لَكُمۡ أَيُّهَ ٱلثَّقَلَانِ

እናንተ ሁለት ከባዶች (ሰዎችና ጋኔኖች) ሆይ! ለእናንተ (መቆጣጠር) በእርግጥ እናስባለን፡፡
Surah Ar-Rahman, Verse 31


فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ
Surah Ar-Rahman, Verse 32


يَٰمَعۡشَرَ ٱلۡجِنِّ وَٱلۡإِنسِ إِنِ ٱسۡتَطَعۡتُمۡ أَن تَنفُذُواْ مِنۡ أَقۡطَارِ ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلۡأَرۡضِ فَٱنفُذُواْۚ لَا تَنفُذُونَ إِلَّا بِسُلۡطَٰنٖ

የጋኔንና የሰው ጭፍሮች ሆይ! ከሰማያትና ከምድር ቀበሌዎች መውጣትን ብትችሉ ውጡ፡፡ በስልጣን እንጅ አትወጡም፡፡ (ግን ስልጣን የላችሁም)
Surah Ar-Rahman, Verse 33


فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ
Surah Ar-Rahman, Verse 34


يُرۡسَلُ عَلَيۡكُمَا شُوَاظٞ مِّن نَّارٖ وَنُحَاسٞ فَلَا تَنتَصِرَانِ

በሁለታችሁም ላይ ከእሳት ነበልባል፣ ጭስም ይላክባችኋል፡፡ (ሁለታችሁም) አትርረዱምም፡፡
Surah Ar-Rahman, Verse 35


فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ
Surah Ar-Rahman, Verse 36


فَإِذَا ٱنشَقَّتِ ٱلسَّمَآءُ فَكَانَتۡ وَرۡدَةٗ كَٱلدِّهَانِ

ሰማይም በተሰነጠቀችና እንደ ጽጌረዳ፣ እንደታረበ ቆዳ በኾነች ጊዜ፤ (ጭንቁን ምን አበረታው)፡፡
Surah Ar-Rahman, Verse 37


فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ
Surah Ar-Rahman, Verse 38


فَيَوۡمَئِذٖ لَّا يُسۡـَٔلُ عَن ذَنۢبِهِۦٓ إِنسٞ وَلَا جَآنّٞ

በዚያም ቀን ሰውም ጃንም ከኃጢኣቱ ገና አይጠየቅም፡፡
Surah Ar-Rahman, Verse 39


فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ
Surah Ar-Rahman, Verse 40


يُعۡرَفُ ٱلۡمُجۡرِمُونَ بِسِيمَٰهُمۡ فَيُؤۡخَذُ بِٱلنَّوَٰصِي وَٱلۡأَقۡدَامِ

ከሓዲዎች በምልክታቸው ይታወቃሉ፡፡ አናቶቻቸውንና ጫማዎቻቸውንም ይያዛሉ፡፡
Surah Ar-Rahman, Verse 41


فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ፡፡
Surah Ar-Rahman, Verse 42


هَٰذِهِۦ جَهَنَّمُ ٱلَّتِي يُكَذِّبُ بِهَا ٱلۡمُجۡرِمُونَ

ይህቺ ያቺ አመጸኞች በእርሷ ያስተባብሉባት የነበረችው ገሀነም ናት (ይባላሉ)፡፡
Surah Ar-Rahman, Verse 43


يَطُوفُونَ بَيۡنَهَا وَبَيۡنَ حَمِيمٍ ءَانٖ

በእርሷና በጣም ሞቃት በኾነ ፍል ውሃ መካከል ይመላለሳሉ፡፡
Surah Ar-Rahman, Verse 44


فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ
Surah Ar-Rahman, Verse 45


وَلِمَنۡ خَافَ مَقَامَ رَبِّهِۦ جَنَّتَانِ

በጌታውም ፊት መቆምን ለፈራ ሰው ሁለት ገነቶች አልሉት፡፡
Surah Ar-Rahman, Verse 46


فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ
Surah Ar-Rahman, Verse 47


ذَوَاتَآ أَفۡنَانٖ

የቀንዘሎች ባለ ቤቶች የኾኑ (ገነቶች አልሉት)፡፡
Surah Ar-Rahman, Verse 48


فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ
Surah Ar-Rahman, Verse 49


فِيهِمَا عَيۡنَانِ تَجۡرِيَانِ

በሁለቱ ውስጥ የሚፈስሱ ሁለት ምንጮች አልሉ፡፡
Surah Ar-Rahman, Verse 50


فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ
Surah Ar-Rahman, Verse 51


فِيهِمَا مِن كُلِّ فَٰكِهَةٖ زَوۡجَانِ

በሁለቱ ውስጥ ከፍራፍሬዎች ሁሉ ሁለት ዓይነቶች (እርጥብና ደረቅ) አልሉ፡፡
Surah Ar-Rahman, Verse 52


فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ
Surah Ar-Rahman, Verse 53


مُتَّكِـِٔينَ عَلَىٰ فُرُشِۭ بَطَآئِنُهَا مِنۡ إِسۡتَبۡرَقٖۚ وَجَنَى ٱلۡجَنَّتَيۡنِ دَانٖ

የውስጥ ጉስጉሳቸው ከወፍራም ሐር በኾኑ ምንጣፎች ላይ የተመቻቹ ሲኾኑ (ይንፈላሰሳሉ)፡፡ የሁለቱም ገነቶች ፍሬ (ለለቃሚ) ቅርብ ነው፡፡
Surah Ar-Rahman, Verse 54


فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ
Surah Ar-Rahman, Verse 55


فِيهِنَّ قَٰصِرَٰتُ ٱلطَّرۡفِ لَمۡ يَطۡمِثۡهُنَّ إِنسٞ قَبۡلَهُمۡ وَلَا جَآنّٞ

በውስጣቸው ከበፊታቸው (ከባሎቻቸው በፊት) ሰውም ጃንም ያልገሰሳቸው ዓይኖቻቸውን (በባሎቻቸው ላይ) አሳጣሪዎች (ሴቶች) አልሉ፡፡
Surah Ar-Rahman, Verse 56


فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ
Surah Ar-Rahman, Verse 57


كَأَنَّهُنَّ ٱلۡيَاقُوتُ وَٱلۡمَرۡجَانُ

ልክ ያቁትና መርጃን ይመስላሉ፡፡
Surah Ar-Rahman, Verse 58


فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ

ከጌታችሁም ጸጋዎቸ በየትኛው ታስተባብላላችሁ
Surah Ar-Rahman, Verse 59


هَلۡ جَزَآءُ ٱلۡإِحۡسَٰنِ إِلَّا ٱلۡإِحۡسَٰنُ

የበጎ ሥራ ዋጋ በጎ እንጅ ሌላ ነውን
Surah Ar-Rahman, Verse 60


فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ
Surah Ar-Rahman, Verse 61


وَمِن دُونِهِمَا جَنَّتَانِ

ከሁለቱ ገነቶችም ሌላ ሁለት ገነቶች አልሉ፡፡
Surah Ar-Rahman, Verse 62


فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?›
Surah Ar-Rahman, Verse 63


مُدۡهَآمَّتَانِ

ከልምላሜያቸው የተነሳ ወደ ጥቁረት ያዘነበሉ ናቸው፡፡
Surah Ar-Rahman, Verse 64


فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ
Surah Ar-Rahman, Verse 65


فِيهِمَا عَيۡنَانِ نَضَّاخَتَانِ

በውስጣቸው ሁለት የሚንፏፉ ምንጮች አልሉ፡፡
Surah Ar-Rahman, Verse 66


فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ
Surah Ar-Rahman, Verse 67


فِيهِمَا فَٰكِهَةٞ وَنَخۡلٞ وَرُمَّانٞ

በውስጣቸው ፍራፍሬ፣ ዘምባባም፣ ሩማንም አልለ፡፡
Surah Ar-Rahman, Verse 68


فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ
Surah Ar-Rahman, Verse 69


فِيهِنَّ خَيۡرَٰتٌ حِسَانٞ

በውስጣቸው ጠባየ መልካሞች መልክ ውቦች (ሴቶች) አልሉ፡፡
Surah Ar-Rahman, Verse 70


فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ
Surah Ar-Rahman, Verse 71


حُورٞ مَّقۡصُورَٰتٞ فِي ٱلۡخِيَامِ

በድንኳኖች ውስጥ የተጨጎሉ የዓይኖቻቸው ጥቁረትና ንጣት ደማቅ የኾኑ ናቸው፡፡
Surah Ar-Rahman, Verse 72


فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ
Surah Ar-Rahman, Verse 73


لَمۡ يَطۡمِثۡهُنَّ إِنسٞ قَبۡلَهُمۡ وَلَا جَآنّٞ

ከነርሱ በፊት ሰውም ጃንም አልገሰሳቸውም፡፡
Surah Ar-Rahman, Verse 74


فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባበላላችሁ
Surah Ar-Rahman, Verse 75


مُتَّكِـِٔينَ عَلَىٰ رَفۡرَفٍ خُضۡرٖ وَعَبۡقَرِيٍّ حِسَانٖ

በሚያረገርጉ አረንጓዴ ምንጣፎችና በሚያማምሩ ስጋጃዎች ላይ የተደላደሉ ሲኾኑ (ይቀመጣሉ)፡፡
Surah Ar-Rahman, Verse 76


فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ
Surah Ar-Rahman, Verse 77


تَبَٰرَكَ ٱسۡمُ رَبِّكَ ذِي ٱلۡجَلَٰلِ وَٱلۡإِكۡرَامِ

የግርማና የመክበር ባለቤት የኾነው ጌታህ ስም ተባረከ፡፡
Surah Ar-Rahman, Verse 78


Author: Muhammed Sadiq And Muhammed Sani Habib


<< Surah 54
>> Surah 56

Amharic Translations by other Authors


Amharic Translation By Muhammed Sadiq And Muhammed Sani Habib
Amharic Translation By Muhammed Sadiq And Muhammed Sani Habib
Amharic Translation By Muhammed Sadiq And Muhammed Sani Habib
Popular Areas
Apartments for rent in Dubai Apartments for rent Abu Dhabi Villas for rent in Dubai House for rent Abu Dhabi Apartments for sale in Dubai Apartments for sale in Abu Dhabi Flat for rent Sharjah
Popular Searches
Studios for rent in UAE Apartments for rent in UAE Villas for rent in UAE Apartments for sale in UAE Villas for sale in UAE Land for sale in UAE Dubai Real Estate
Trending Areas
Apartments for rent in Dubai Marina Apartments for sale in Dubai Marina Villa for rent in Sharjah Villa for sale in Dubai Flat for rent in Ajman Studio for rent in Abu Dhabi Villa for rent in Ajman
Trending Searches
Villa for rent in Abu Dhabi Shop for rent in Dubai Villas for sale in Ajman Studio for rent in Sharjah 1 Bedroom Apartment for rent in Dubai Property for rent in Abu Dhabi Commercial properties for sale
© Copyright Dubai Prayer Time. All Rights Reserved
Designed by Prayer Time In Dubai