Surah At-Tariq - Amharic Translation by Muhammed Sadiq And Muhammed Sani Habib
وَٱلسَّمَآءِ وَٱلطَّارِقِ
በሰማዩ በሌሊት መጪውም እምላለሁ፡፡
Surah At-Tariq, Verse 1
وَمَآ أَدۡرَىٰكَ مَا ٱلطَّارِقُ
የሌሊት መጪውም ምን እንደ ኾነ ምን አሳወቀህ
Surah At-Tariq, Verse 2
ٱلنَّجۡمُ ٱلثَّاقِبُ
ጨለማን ቀዳጁ ኮከብ ነው፡፡
Surah At-Tariq, Verse 3
إِن كُلُّ نَفۡسٖ لَّمَّا عَلَيۡهَا حَافِظٞ
ነፍስ ሁሉ በእርሷ ላይ ጠባቂ ያለባት እንጅ ሌላ አይደለችም፡፡
Surah At-Tariq, Verse 4
فَلۡيَنظُرِ ٱلۡإِنسَٰنُ مِمَّ خُلِقَ
ሰውም ከምን እንደተፈጠረ ይመልከት፡፡
Surah At-Tariq, Verse 5
خُلِقَ مِن مَّآءٖ دَافِقٖ
ከተስፈንጣሪ ውሃ ተፈጠረ፡፡
Surah At-Tariq, Verse 6
يَخۡرُجُ مِنۢ بَيۡنِ ٱلصُّلۡبِ وَٱلتَّرَآئِبِ
ከጀርባና ከእርግብግብቶች መካከል የሚወጣ ከኾነ (ውሃ)፡፡
Surah At-Tariq, Verse 7
إِنَّهُۥ عَلَىٰ رَجۡعِهِۦ لَقَادِرٞ
እርሱ (አላህ) በመመለሱ ላይ በእርግጥ ቻይ ነው፡፡
Surah At-Tariq, Verse 8
يَوۡمَ تُبۡلَى ٱلسَّرَآئِرُ
ምስጢሮች በሚገለጡበት ቀን፡፡
Surah At-Tariq, Verse 9
فَمَا لَهُۥ مِن قُوَّةٖ وَلَا نَاصِرٖ
ለእርሱም (ለሰው) ኀይልና ረዳት ምንም የለውም፡፡
Surah At-Tariq, Verse 10
وَٱلسَّمَآءِ ذَاتِ ٱلرَّجۡعِ
የመመለስ ባለቤት በኾነችው ሰማይም እምላለሁ፡፡
Surah At-Tariq, Verse 11
وَٱلۡأَرۡضِ ذَاتِ ٱلصَّدۡعِ
(በበቃይ) የመሰንጠቅ ባለቤት በኾነችው ምድርም፤
Surah At-Tariq, Verse 12
إِنَّهُۥ لَقَوۡلٞ فَصۡلٞ
እርሱ (እውነትን ከውሸት) የሚለይ ቃል ነው፡፡
Surah At-Tariq, Verse 13
وَمَا هُوَ بِٱلۡهَزۡلِ
እርሱም ቀልድ አይደለም፡፡
Surah At-Tariq, Verse 14
إِنَّهُمۡ يَكِيدُونَ كَيۡدٗا
እነርሱ በእርግጥ ተንኮልን ይሠራሉ፡፡
Surah At-Tariq, Verse 15
وَأَكِيدُ كَيۡدٗا
(እኔ) ተንኮልንም እመልሳለሁ፡፡
Surah At-Tariq, Verse 16
فَمَهِّلِ ٱلۡكَٰفِرِينَ أَمۡهِلۡهُمۡ رُوَيۡدَۢا
ከሓዲዎችንም ቀን ስጣቸው፡፡ ጥቂትን ጊዜ አቆያቸው፡፡
Surah At-Tariq, Verse 17