Surah At-Tin - Amharic Translation by Muhammed Sadiq And Muhammed Sani Habib
وَٱلتِّينِ وَٱلزَّيۡتُونِ
በበለስና በዘይት ወይራ እምላለሁ፡፡
Surah At-Tin, Verse 1
وَطُورِ سِينِينَ
በሲኒን ተራራም፤
Surah At-Tin, Verse 2
وَهَٰذَا ٱلۡبَلَدِ ٱلۡأَمِينِ
በዚህ በጸጥተኛው አገርም (እምላለሁ)፡፡
Surah At-Tin, Verse 3
لَقَدۡ خَلَقۡنَا ٱلۡإِنسَٰنَ فِيٓ أَحۡسَنِ تَقۡوِيمٖ
ሰውን በጣም በአማረ አቋም ላይ ፈጠርነው፡፡
Surah At-Tin, Verse 4
ثُمَّ رَدَدۡنَٰهُ أَسۡفَلَ سَٰفِلِينَ
ከዚያም (ከፊሉን) ከዝቅተኞች ሁሉ በታች አድርገን መለስነው፡፡
Surah At-Tin, Verse 5
إِلَّا ٱلَّذِينَ ءَامَنُواْ وَعَمِلُواْ ٱلصَّـٰلِحَٰتِ فَلَهُمۡ أَجۡرٌ غَيۡرُ مَمۡنُونٖ
ግን እነዚያ ያመኑት መልካሞችንም የሠሩት ለእነርሱ ተቆራጭ ያልኾነ ምንዳ አልላቸው፡፡
Surah At-Tin, Verse 6
فَمَا يُكَذِّبُكَ بَعۡدُ بِٱلدِّينِ
ታዲያ ከዚህ በኋላ በፍርዱ ምን አስተባባይ አደረገህ
Surah At-Tin, Verse 7
أَلَيۡسَ ٱللَّهُ بِأَحۡكَمِ ٱلۡحَٰكِمِينَ
አላህ ከፈራጆች ሁሉ ይበልጥ ፈራጅ አይደለምን? (ነው)፡፡
Surah At-Tin, Verse 8