UAE Prayer Times

  • Dubai
  • Abu Dhabi
  • Sharjah
  • Ajman
  • Fujairah
  • Umm Al Quwain
  • Ras Al Khaimah
  • Quran Translations

Surah Al-Haaqqa - Amharic Translation by Muhammed Sadiq And Muhammed Sani Habib


ٱلۡحَآقَّةُ

እውነትን አረጋጋጪቱ (ትንሣኤ)፡፡
Surah Al-Haaqqa, Verse 1


مَا ٱلۡحَآقَّةُ

አረጋጋጪቱም (እርሷ) ምንድን ናት
Surah Al-Haaqqa, Verse 2


وَمَآ أَدۡرَىٰكَ مَا ٱلۡحَآقَّةُ

አረጋጋጪቱም ምን እንደኾነች ምን አሳወቀህ
Surah Al-Haaqqa, Verse 3


كَذَّبَتۡ ثَمُودُ وَعَادُۢ بِٱلۡقَارِعَةِ

ሰሙድና ዓድ በቆርቋሪይቱ (ትንሣኤ) አስተባበሉ፡፡
Surah Al-Haaqqa, Verse 4


فَأَمَّا ثَمُودُ فَأُهۡلِكُواْ بِٱلطَّاغِيَةِ

ሠሙድማ ወሰን በሌላት ጩኸት ተጠፋ፤ (ተወደሙ)፡፡
Surah Al-Haaqqa, Verse 5


وَأَمَّا عَادٞ فَأُهۡلِكُواْ بِرِيحٖ صَرۡصَرٍ عَاتِيَةٖ

ዓድማ በኀይል በምትንሻሻ ብርቱ ነፋስ ተጠፉ፡፡
Surah Al-Haaqqa, Verse 6


سَخَّرَهَا عَلَيۡهِمۡ سَبۡعَ لَيَالٖ وَثَمَٰنِيَةَ أَيَّامٍ حُسُومٗاۖ فَتَرَى ٱلۡقَوۡمَ فِيهَا صَرۡعَىٰ كَأَنَّهُمۡ أَعۡجَازُ نَخۡلٍ خَاوِيَةٖ

ተከታታይ በኾኑ ሰባት ሌሊቶችና ስምንት መዓልቶች ውስጥ በእነርሱ ላይ ለቀቃት፡፡ ሕዝቦቹንም፤ በውስጧ የተጣሉ ኾነው ልክ ክፍት የኾኑ የዘንባባ ግንዶች መስለው ታያቸዋለህ፡፡
Surah Al-Haaqqa, Verse 7


فَهَلۡ تَرَىٰ لَهُم مِّنۢ بَاقِيَةٖ

ለእነርሱም ቀሪን ታያለህን
Surah Al-Haaqqa, Verse 8


وَجَآءَ فِرۡعَوۡنُ وَمَن قَبۡلَهُۥ وَٱلۡمُؤۡتَفِكَٰتُ بِٱلۡخَاطِئَةِ

ፈርዖን ከበፊቱ የነበሩትም ሰዎች ተገልባጮቹም (ከተሞች) በኀጢአት (ሥራዎች) መጡ፡፡
Surah Al-Haaqqa, Verse 9


فَعَصَوۡاْ رَسُولَ رَبِّهِمۡ فَأَخَذَهُمۡ أَخۡذَةٗ رَّابِيَةً

የጌታቸውንም መልእክተኛ ትዕዛዝ ጣሱ፡፡ የበረታችንም አያያዝ ያዛቸው፡፡
Surah Al-Haaqqa, Verse 10


إِنَّا لَمَّا طَغَا ٱلۡمَآءُ حَمَلۡنَٰكُمۡ فِي ٱلۡجَارِيَةِ

እኛ ውሃው ባየለ ጊዜ በተንሻላይቱ ታንኳ ውስጥ ጫንናችሁ፡፡
Surah Al-Haaqqa, Verse 11


لِنَجۡعَلَهَا لَكُمۡ تَذۡكِرَةٗ وَتَعِيَهَآ أُذُنٞ وَٰعِيَةٞ

ለእናንተ መገሰጫ ልናደርጋት አጥኒ የኾነችም ጆሮ ታጠናት ዘንድ፡፡
Surah Al-Haaqqa, Verse 12


فَإِذَا نُفِخَ فِي ٱلصُّورِ نَفۡخَةٞ وَٰحِدَةٞ

በቀንዱም አንዲት መንነፋት በተነፋች ጊዜ፡፡
Surah Al-Haaqqa, Verse 13


وَحُمِلَتِ ٱلۡأَرۡضُ وَٱلۡجِبَالُ فَدُكَّتَا دَكَّةٗ وَٰحِدَةٗ

ምድርና ጋራዎችም (ከስፍራቸው) በተነሱና አንዲትን መሰባበር በተሰባበሩ ጊዜ፡፡
Surah Al-Haaqqa, Verse 14


فَيَوۡمَئِذٖ وَقَعَتِ ٱلۡوَاقِعَةُ

በዚያ ቀን ኋኝቱ (ትንሣኤ) ትኾናለች፡፡
Surah Al-Haaqqa, Verse 15


وَٱنشَقَّتِ ٱلسَّمَآءُ فَهِيَ يَوۡمَئِذٖ وَاهِيَةٞ

ሰማይም ትቀደዳለች፡፡ ስለዚህ እርሷ በዚያ ቀን ደካማ ናት፡፡
Surah Al-Haaqqa, Verse 16


وَٱلۡمَلَكُ عَلَىٰٓ أَرۡجَآئِهَاۚ وَيَحۡمِلُ عَرۡشَ رَبِّكَ فَوۡقَهُمۡ يَوۡمَئِذٖ ثَمَٰنِيَةٞ

መላእክትም በየጫፎችዋ ላይ ይኾናሉ፡፡ የጌታህንም ዐርሽ በዚያ ቀን ስምንት መላእክት ከበላያቸው ይሸከማሉ፡፡
Surah Al-Haaqqa, Verse 17


يَوۡمَئِذٖ تُعۡرَضُونَ لَا تَخۡفَىٰ مِنكُمۡ خَافِيَةٞ

በዚያ ቀን ከእናንተ ተደባቂ (ነገሮች) የማይደበቁ ሲኾኑ ትቅቀረባላችሁ፡፡
Surah Al-Haaqqa, Verse 18


فَأَمَّا مَنۡ أُوتِيَ كِتَٰبَهُۥ بِيَمِينِهِۦ فَيَقُولُ هَآؤُمُ ٱقۡرَءُواْ كِتَٰبِيَهۡ

መጽሐፉን በቀኙ የተሰጠ ሰውማ (ለጓደኞቹ) «እንኩ፤ መጽሐፌን አንብቡ» ይላል፡፡
Surah Al-Haaqqa, Verse 19


إِنِّي ظَنَنتُ أَنِّي مُلَٰقٍ حِسَابِيَهۡ

«እኔ ምርመራየን የምገናኝ መኾኔን አረጋገጥኩ፤» (ተዘጋጀሁም ይላል)፡፡
Surah Al-Haaqqa, Verse 20


فَهُوَ فِي عِيشَةٖ رَّاضِيَةٖ

እርሱም በተወደደች ኑሮ ውሰጥ ይኾናል፡፡
Surah Al-Haaqqa, Verse 21


فِي جَنَّةٍ عَالِيَةٖ

በከፍተኛይቱ ገነት ውስጥ፡፡
Surah Al-Haaqqa, Verse 22


قُطُوفُهَا دَانِيَةٞ

ፍሬዎችዋ ቅርቦች የኾኑ፡፡
Surah Al-Haaqqa, Verse 23


كُلُواْ وَٱشۡرَبُواْ هَنِيٓـَٔۢا بِمَآ أَسۡلَفۡتُمۡ فِي ٱلۡأَيَّامِ ٱلۡخَالِيَةِ

በአለፉት ቀናት ውስጥ (በምድረ ዓለም) ባስቀደማችሁት ምክንያት ብሉ፤ ጠጡም፤ (ይባላሉ)፡፡
Surah Al-Haaqqa, Verse 24


وَأَمَّا مَنۡ أُوتِيَ كِتَٰبَهُۥ بِشِمَالِهِۦ فَيَقُولُ يَٰلَيۡتَنِي لَمۡ أُوتَ كِتَٰبِيَهۡ

መጽሐፉንም በግራው የተሰጠማ «ዋ ጥፋቴ! ምነው መጽሐፌን ባልተሰጠሁ» ይላል፡፡
Surah Al-Haaqqa, Verse 25


وَلَمۡ أَدۡرِ مَا حِسَابِيَهۡ

«ምርመራየንም ምን እንደኾነ ባላወቅኩ፡፡
Surah Al-Haaqqa, Verse 26


يَٰلَيۡتَهَا كَانَتِ ٱلۡقَاضِيَةَ

«እርሷ (ሞት ሕይወቴን) ምነው ፈጻሚ በኾነች፡፡
Surah Al-Haaqqa, Verse 27


مَآ أَغۡنَىٰ عَنِّي مَالِيَهۡۜ

«ገንዘቤ ከእኔ ምንንም አላብቃቃኝ፤ (አልጠቀመኝም)፡፡
Surah Al-Haaqqa, Verse 28


هَلَكَ عَنِّي سُلۡطَٰنِيَهۡ

«ኀይሌ ከእኔ ላይ ጠፋ» (ይላል)፡፡
Surah Al-Haaqqa, Verse 29


خُذُوهُ فَغُلُّوهُ

«ያዙት፤ እሰሩትም፡፡
Surah Al-Haaqqa, Verse 30


ثُمَّ ٱلۡجَحِيمَ صَلُّوهُ

«ከዚያም በእሳት ውሰጥ አግቡት፡፡
Surah Al-Haaqqa, Verse 31


ثُمَّ فِي سِلۡسِلَةٖ ذَرۡعُهَا سَبۡعُونَ ذِرَاعٗا فَٱسۡلُكُوهُ

«ከዚያም ርዝመቷ ሰባ ክንድ በኾነች ሰንሰለት ውስጥ አግቡት፡፡»
Surah Al-Haaqqa, Verse 32


إِنَّهُۥ كَانَ لَا يُؤۡمِنُ بِٱللَّهِ ٱلۡعَظِيمِ

እርሱ ታላቅ በኾነው አላህ አያምንም ነበርና፡፡
Surah Al-Haaqqa, Verse 33


وَلَا يَحُضُّ عَلَىٰ طَعَامِ ٱلۡمِسۡكِينِ

ድኾችንም በማብላት ላይ አያግባባም ነበርና፡፡
Surah Al-Haaqqa, Verse 34


فَلَيۡسَ لَهُ ٱلۡيَوۡمَ هَٰهُنَا حَمِيمٞ

ለእርሱም ዛሬ እዚህ ዘመድ የለውም፡፡
Surah Al-Haaqqa, Verse 35


وَلَا طَعَامٌ إِلَّا مِنۡ غِسۡلِينٖ

ምግብም ከእሳት ሰዎች ቁስል እጣቢ (እዥ) በስተቀር የለውም፡፡
Surah Al-Haaqqa, Verse 36


لَّا يَأۡكُلُهُۥٓ إِلَّا ٱلۡخَٰطِـُٔونَ

ኀጢኣተኞች እንጅ ሌላ አይበላውም፤ (ይባላል)፡፡
Surah Al-Haaqqa, Verse 37


فَلَآ أُقۡسِمُ بِمَا تُبۡصِرُونَ

በምታዩትም ነገር እምላለሁ፡፡
Surah Al-Haaqqa, Verse 38


وَمَا لَا تُبۡصِرُونَ

በማታዩትም ነገር፡፡
Surah Al-Haaqqa, Verse 39


إِنَّهُۥ لَقَوۡلُ رَسُولٖ كَرِيمٖ

እርሱ (ቁርኣን) የተከበረ መልክተኛ ቃል ነው፡፡
Surah Al-Haaqqa, Verse 40


وَمَا هُوَ بِقَوۡلِ شَاعِرٖۚ قَلِيلٗا مَّا تُؤۡمِنُونَ

እርሱም የባለቅኔ ቃል (ግጥም) አይደለም፡፡ ጥቂትን ብቻ ታምናላችሁ፡፡
Surah Al-Haaqqa, Verse 41


وَلَا بِقَوۡلِ كَاهِنٖۚ قَلِيلٗا مَّا تَذَكَّرُونَ

የጠንቋይም ቃል አይደለም፡፡ ጥቂትን ብቻ ታስታውሳላችሁ፡፡
Surah Al-Haaqqa, Verse 42


تَنزِيلٞ مِّن رَّبِّ ٱلۡعَٰلَمِينَ

ከዓለማት ጌታ የተወረደ ነው፡፡
Surah Al-Haaqqa, Verse 43


وَلَوۡ تَقَوَّلَ عَلَيۡنَا بَعۡضَ ٱلۡأَقَاوِيلِ

በእኛ ላይም ከፊልን ቃላት (ያላልነውን) በቀጠፈ ኖሮ፤
Surah Al-Haaqqa, Verse 44


لَأَخَذۡنَا مِنۡهُ بِٱلۡيَمِينِ

በኀይል በያዝነው ነበር፡፡
Surah Al-Haaqqa, Verse 45


ثُمَّ لَقَطَعۡنَا مِنۡهُ ٱلۡوَتِينَ

ከዚያም ከእርሱ የልቡን ሥር (የተንጠለጠለበትን ጅማት) በቆረጥን ነበር፡፡
Surah Al-Haaqqa, Verse 46


فَمَا مِنكُم مِّنۡ أَحَدٍ عَنۡهُ حَٰجِزِينَ

ከእናንተም ውስጥ ከእርሱ ላይ ከልካዮች ምንም አይኖሩም፡፡
Surah Al-Haaqqa, Verse 47


وَإِنَّهُۥ لَتَذۡكِرَةٞ لِّلۡمُتَّقِينَ

እርሱም (ቁርኣን) ለጥንቁቆቹ መገሠጫ ነው፡፡
Surah Al-Haaqqa, Verse 48


وَإِنَّا لَنَعۡلَمُ أَنَّ مِنكُم مُّكَذِّبِينَ

እኛም ከእናንተ ውስጥ አስተባባዮች መኖራቸውን በእርግጥ እናውቃለን፡፡
Surah Al-Haaqqa, Verse 49


وَإِنَّهُۥ لَحَسۡرَةٌ عَلَى ٱلۡكَٰفِرِينَ

እርሱም (ቁርኣን) በከሓዲዎቹ ላይ ጸጸት ነው፡፡
Surah Al-Haaqqa, Verse 50


وَإِنَّهُۥ لَحَقُّ ٱلۡيَقِينِ

እርሱም የተረጋገጠ እውነት ነው፡፡
Surah Al-Haaqqa, Verse 51


فَسَبِّحۡ بِٱسۡمِ رَبِّكَ ٱلۡعَظِيمِ

የታላቁን ጌታህንም ስም አወድስ፡፡
Surah Al-Haaqqa, Verse 52


Author: Muhammed Sadiq And Muhammed Sani Habib


<< Surah 68
>> Surah 70

Amharic Translations by other Authors


Amharic Translation By Muhammed Sadiq And Muhammed Sani Habib
Amharic Translation By Muhammed Sadiq And Muhammed Sani Habib
Amharic Translation By Muhammed Sadiq And Muhammed Sani Habib
Popular Areas
Apartments for rent in Dubai Apartments for rent Abu Dhabi Villas for rent in Dubai House for rent Abu Dhabi Apartments for sale in Dubai Apartments for sale in Abu Dhabi Flat for rent Sharjah
Popular Searches
Studios for rent in UAE Apartments for rent in UAE Villas for rent in UAE Apartments for sale in UAE Villas for sale in UAE Land for sale in UAE Dubai Real Estate
Trending Areas
Apartments for rent in Dubai Marina Apartments for sale in Dubai Marina Villa for rent in Sharjah Villa for sale in Dubai Flat for rent in Ajman Studio for rent in Abu Dhabi Villa for rent in Ajman
Trending Searches
Villa for rent in Abu Dhabi Shop for rent in Dubai Villas for sale in Ajman Studio for rent in Sharjah 1 Bedroom Apartment for rent in Dubai Property for rent in Abu Dhabi Commercial properties for sale
© Copyright Dubai Prayer Time. All Rights Reserved
Designed by Prayer Time In Dubai