UAE Prayer Times

  • Dubai
  • Abu Dhabi
  • Sharjah
  • Ajman
  • Fujairah
  • Umm Al Quwain
  • Ras Al Khaimah
  • Quran Translations

Surah Al-Maarij - Amharic Translation by Muhammed Sadiq And Muhammed Sani Habib


سَأَلَ سَآئِلُۢ بِعَذَابٖ وَاقِعٖ

ወዳቂ ከኾነው ቅጣት ጠያቂ ጠየቀ፡፡
Surah Al-Maarij, Verse 1


لِّلۡكَٰفِرِينَ لَيۡسَ لَهُۥ دَافِعٞ

በከሓዲዎች ላይ (ወዳቂ ከኾነው) ለእርሱ መላሽ የለውም፡፡
Surah Al-Maarij, Verse 2


مِّنَ ٱللَّهِ ذِي ٱلۡمَعَارِجِ

የ(ሰማያት) መሰላሎች ባለቤት ከኾነው አላህ (መላሽ የለውም)፡፡
Surah Al-Maarij, Verse 3


تَعۡرُجُ ٱلۡمَلَـٰٓئِكَةُ وَٱلرُّوحُ إِلَيۡهِ فِي يَوۡمٖ كَانَ مِقۡدَارُهُۥ خَمۡسِينَ أَلۡفَ سَنَةٖ

መላእክቱና መንፈሱም ልኩ አምሳ ሺሕ ዓመት በኾነ ቀን ውስጥ ወደእርሱ ያርጋሉ፤ (ይወጣሉ)፡፡
Surah Al-Maarij, Verse 4


فَٱصۡبِرۡ صَبۡرٗا جَمِيلًا

መልካምንም ትዕግስት ታገሥ፡፡
Surah Al-Maarij, Verse 5


إِنَّهُمۡ يَرَوۡنَهُۥ بَعِيدٗا

እነርሱ (ያንን ቀን) ሩቅ አድርገው ያዩታል፡፡
Surah Al-Maarij, Verse 6


وَنَرَىٰهُ قَرِيبٗا

እኛም ቅርብ ኾኖ እናየዋለን፡፡
Surah Al-Maarij, Verse 7


يَوۡمَ تَكُونُ ٱلسَّمَآءُ كَٱلۡمُهۡلِ

ሰማይ እንደ ዘይት አተላ በምትኾንበት ቀን፡፡
Surah Al-Maarij, Verse 8


وَتَكُونُ ٱلۡجِبَالُ كَٱلۡعِهۡنِ

ጋራዎችም በተለያዩ ቀለማት እንደ ተነከረ ሱፍ (ነፋስ እንደሚያበረው) በሚኾኑበት ቀን፡፡
Surah Al-Maarij, Verse 9


وَلَا يَسۡـَٔلُ حَمِيمٌ حَمِيمٗا

ዘመድም ዘመድን በማይጠይቅበት ቀን፤ (መላሽ የለውም)፡፡
Surah Al-Maarij, Verse 10


يُبَصَّرُونَهُمۡۚ يَوَدُّ ٱلۡمُجۡرِمُ لَوۡ يَفۡتَدِي مِنۡ عَذَابِ يَوۡمِئِذِۭ بِبَنِيهِ

(ዘመዶቻቸውን) ያዩዋቸዋል፡፡ አመጸኛው ከዚያ ቀን ስቃይ (ነፍሱን) በልጆቹ ሊበዥ ይመኛል፡፡
Surah Al-Maarij, Verse 11


وَصَٰحِبَتِهِۦ وَأَخِيهِ

በሚስቱም በወንድሙም፡፡
Surah Al-Maarij, Verse 12


وَفَصِيلَتِهِ ٱلَّتِي تُـٔۡوِيهِ

በዚያችም በምታስጠጋው ጎሳው፡፡
Surah Al-Maarij, Verse 13


وَمَن فِي ٱلۡأَرۡضِ جَمِيعٗا ثُمَّ يُنجِيهِ

በምድርም ላይ ባለው ሁሉ (ሊበዥ) ከዚያም ሊያድነው (ይመኛል)፡፡
Surah Al-Maarij, Verse 14


كَلَّآۖ إِنَّهَا لَظَىٰ

ይተው! እርሷ (እሳቲቱ) ለዟ ናት፡፡
Surah Al-Maarij, Verse 15


نَزَّاعَةٗ لِّلشَّوَىٰ

የራስን ቅል ቆዳ የምትሞሽልቅ ስትኾን፡፡
Surah Al-Maarij, Verse 16


تَدۡعُواْ مَنۡ أَدۡبَرَ وَتَوَلَّىٰ

(ከእምነት) የዞረንና የሸሸን ሰው (ወደእርሷ) ትጠራለች፡፡
Surah Al-Maarij, Verse 17


وَجَمَعَ فَأَوۡعَىٰٓ

ገንዘብን የሰበሰበንና (ዘካውን ሳይሰጥ) የቆጠረንም፤ (ትጠራለች)፡፡
Surah Al-Maarij, Verse 18


۞إِنَّ ٱلۡإِنسَٰنَ خُلِقَ هَلُوعًا

ሰው ቅጠ ቢስ ኾኖ ተፈጠረ፡፡
Surah Al-Maarij, Verse 19


إِذَا مَسَّهُ ٱلشَّرُّ جَزُوعٗا

ክፉ ነገር ባገኘው ጊዜ ብስጪተኛ፡፡
Surah Al-Maarij, Verse 20


وَإِذَا مَسَّهُ ٱلۡخَيۡرُ مَنُوعًا

መልካምም ነገር (ድሎት) ባገኘ ጊዜ ከልካይ (ኾኖ ተፈጠረ)፡፡
Surah Al-Maarij, Verse 21


إِلَّا ٱلۡمُصَلِّينَ

ሰጋጆቹ ብቻ ሲቀሩ፡፡
Surah Al-Maarij, Verse 22


ٱلَّذِينَ هُمۡ عَلَىٰ صَلَاتِهِمۡ دَآئِمُونَ

እነዚያ እነርሱ በስግደታቸው ላይ ዘውታሪዎች የኾኑት፡፡
Surah Al-Maarij, Verse 23


وَٱلَّذِينَ فِيٓ أَمۡوَٰلِهِمۡ حَقّٞ مَّعۡلُومٞ

እነዚያም በገንዘቦቻቸው ላይ የታወቀ መብት ያለባቸው የኾኑት፡፡
Surah Al-Maarij, Verse 24


لِّلسَّآئِلِ وَٱلۡمَحۡرُومِ

ለለማኝ ከልመና ለሚከለከልም (መብት ያለባቸው የኾኑት)፡፡
Surah Al-Maarij, Verse 25


وَٱلَّذِينَ يُصَدِّقُونَ بِيَوۡمِ ٱلدِّينِ

እነዚያም በፍርዱ ቀን እውነት የሚሉት (የሚያረጋግጡት)፡፡
Surah Al-Maarij, Verse 26


وَٱلَّذِينَ هُم مِّنۡ عَذَابِ رَبِّهِم مُّشۡفِقُونَ

እነዚያም እነርሱ ከጌታቸው ቅጣት ፈሪዎች የኾኑት፡፡
Surah Al-Maarij, Verse 27


إِنَّ عَذَابَ رَبِّهِمۡ غَيۡرُ مَأۡمُونٖ

የጌታቸው ቅጣት (መምጣቱ) የማያስተማምን ነውና፡፡
Surah Al-Maarij, Verse 28


وَٱلَّذِينَ هُمۡ لِفُرُوجِهِمۡ حَٰفِظُونَ

እነዚያም እነርሱ ብልቶቻቸውን ጠባቂዎች የኾኑት፡፡
Surah Al-Maarij, Verse 29


إِلَّا عَلَىٰٓ أَزۡوَٰجِهِمۡ أَوۡ مَا مَلَكَتۡ أَيۡمَٰنُهُمۡ فَإِنَّهُمۡ غَيۡرُ مَلُومِينَ

በሚስቶቻቸው ወይም እጆቻቸው በያዙዋቸው (ባሪያዎች) ላይ ሲቀር፡፡ እነርሱ (በእነዚህ) የማይወቀሱ ናቸውና፡፡
Surah Al-Maarij, Verse 30


فَمَنِ ٱبۡتَغَىٰ وَرَآءَ ذَٰلِكَ فَأُوْلَـٰٓئِكَ هُمُ ٱلۡعَادُونَ

ከዚያም ወዲያ የፈለገ ሰው እነዚያ እነሱ ድንበር አላፊዎች ናቸው፡፡
Surah Al-Maarij, Verse 31


وَٱلَّذِينَ هُمۡ لِأَمَٰنَٰتِهِمۡ وَعَهۡدِهِمۡ رَٰعُونَ

እነዚያም እነርሱ አደራዎቻቸውንና ቃል ኪዳናቸውን ጠባቂዎች የኾኑት፡፡
Surah Al-Maarij, Verse 32


وَٱلَّذِينَ هُم بِشَهَٰدَٰتِهِمۡ قَآئِمُونَ

እነዚያም እነርሱ በምስክርነታቸው ትክክለኞች የኾኑት፡፡
Surah Al-Maarij, Verse 33


وَٱلَّذِينَ هُمۡ عَلَىٰ صَلَاتِهِمۡ يُحَافِظُونَ

እነዚያም እነርሱ በሶላቶቻቸው ላይ የሚጠባበቁት፡፡
Surah Al-Maarij, Verse 34


أُوْلَـٰٓئِكَ فِي جَنَّـٰتٖ مُّكۡرَمُونَ

እነዚህ (ከዚህ በላይ የተወሱት ሁሉ) በገነቶች ውስጥ የሚከበሩ ናቸው፡፡
Surah Al-Maarij, Verse 35


فَمَالِ ٱلَّذِينَ كَفَرُواْ قِبَلَكَ مُهۡطِعِينَ

ለእነዚያም ለካዱት ወደ አንተ በኩል አንገቶቻቸውን መዝዘው የሚያተኩሩት ምን አላቸው
Surah Al-Maarij, Verse 36


عَنِ ٱلۡيَمِينِ وَعَنِ ٱلشِّمَالِ عِزِينَ

ከቀኝና ከግራ ክፍልፍል ጭፍሮች ሲኾኑ፡፡
Surah Al-Maarij, Verse 37


أَيَطۡمَعُ كُلُّ ٱمۡرِيٕٖ مِّنۡهُمۡ أَن يُدۡخَلَ جَنَّةَ نَعِيمٖ

ከእነርሱ እያንዳንዱ ሰው የጸጋይቱን ገነት መግባትን ይከጅላልን
Surah Al-Maarij, Verse 38


كَلَّآۖ إِنَّا خَلَقۡنَٰهُم مِّمَّا يَعۡلَمُونَ

ይከልከል፤ እኛ ከሚያውቁት ነገር (ከፍቶት ጠብታ) ፈጠርናቸው፡፡
Surah Al-Maarij, Verse 39


فَلَآ أُقۡسِمُ بِرَبِّ ٱلۡمَشَٰرِقِ وَٱلۡمَغَٰرِبِ إِنَّا لَقَٰدِرُونَ

በምሥራቆችና በምዕራቦችም ጌታ እምላለሁ፡፡ እኛ በእርግጥ ቻዮች ነን፡፡
Surah Al-Maarij, Verse 40


عَلَىٰٓ أَن نُّبَدِّلَ خَيۡرٗا مِّنۡهُمۡ وَمَا نَحۡنُ بِمَسۡبُوقِينَ

ከእነርሱ የተሻለን በመለወጥ ላይ፡፡ እኛም ተሸናፊዎች አይደለንም፡፡
Surah Al-Maarij, Verse 41


فَذَرۡهُمۡ يَخُوضُواْ وَيَلۡعَبُواْ حَتَّىٰ يُلَٰقُواْ يَوۡمَهُمُ ٱلَّذِي يُوعَدُونَ

ያንንም የሚስፈራሩበትን ቀናቸውን እስከሚገናኙ ድረስ ተዋቸው፡፡ ይዋኙ ይጫወቱም፡፡
Surah Al-Maarij, Verse 42


يَوۡمَ يَخۡرُجُونَ مِنَ ٱلۡأَجۡدَاثِ سِرَاعٗا كَأَنَّهُمۡ إِلَىٰ نُصُبٖ يُوفِضُونَ

ወደ ጣዖቶች እንደሚሽቀዳደሙ ኾነው ከመቃብሮቻቸው ፈጥነው የሚወጡበትን ቀን (እስከሚገናኙ ድረስ ተዋቸው)፡፡
Surah Al-Maarij, Verse 43


خَٰشِعَةً أَبۡصَٰرُهُمۡ تَرۡهَقُهُمۡ ذِلَّةٞۚ ذَٰلِكَ ٱلۡيَوۡمُ ٱلَّذِي كَانُواْ يُوعَدُونَ

ዓይኖቻቸው ያፈሩ ኾነው ውርደት ትሸፍናቸዋለች፡፡ ይህ ቀን ያ ይስፈራሩበት የነበሩት ነው፡፡
Surah Al-Maarij, Verse 44


Author: Muhammed Sadiq And Muhammed Sani Habib


<< Surah 69
>> Surah 71

Amharic Translations by other Authors


Amharic Translation By Muhammed Sadiq And Muhammed Sani Habib
Amharic Translation By Muhammed Sadiq And Muhammed Sani Habib
Amharic Translation By Muhammed Sadiq And Muhammed Sani Habib
Popular Areas
Apartments for rent in Dubai Apartments for rent Abu Dhabi Villas for rent in Dubai House for rent Abu Dhabi Apartments for sale in Dubai Apartments for sale in Abu Dhabi Flat for rent Sharjah
Popular Searches
Studios for rent in UAE Apartments for rent in UAE Villas for rent in UAE Apartments for sale in UAE Villas for sale in UAE Land for sale in UAE Dubai Real Estate
Trending Areas
Apartments for rent in Dubai Marina Apartments for sale in Dubai Marina Villa for rent in Sharjah Villa for sale in Dubai Flat for rent in Ajman Studio for rent in Abu Dhabi Villa for rent in Ajman
Trending Searches
Villa for rent in Abu Dhabi Shop for rent in Dubai Villas for sale in Ajman Studio for rent in Sharjah 1 Bedroom Apartment for rent in Dubai Property for rent in Abu Dhabi Commercial properties for sale
© Copyright Dubai Prayer Time. All Rights Reserved
Designed by Prayer Time In Dubai