Surah Al-Muddathir - Amharic Translation by Muhammed Sadiq And Muhammed Sani Habib
يَـٰٓأَيُّهَا ٱلۡمُدَّثِّرُ
አንተ (ልብስህን) ደራቢው ሆይ
Surah Al-Muddathir, Verse 1
قُمۡ فَأَنذِرۡ
ተነሳ አስጠንቅቅም፡፡
Surah Al-Muddathir, Verse 2
وَرَبَّكَ فَكَبِّرۡ
ጌታህንም አክብር፡፡
Surah Al-Muddathir, Verse 3
وَثِيَابَكَ فَطَهِّرۡ
ልብስህንም አጥራ፡፡
Surah Al-Muddathir, Verse 4
وَٱلرُّجۡزَ فَٱهۡجُرۡ
ጣዖትንም ራቅ፡፡
Surah Al-Muddathir, Verse 5
وَلَا تَمۡنُن تَسۡتَكۡثِرُ
ማብዛትንም የምትፈልግ ኾነህ፤ (በረከትን) አትለግስለለ
Surah Al-Muddathir, Verse 6
وَلِرَبِّكَ فَٱصۡبِرۡ
ለጌታህም (ትዕዛዝ) ታገሥ፡፡
Surah Al-Muddathir, Verse 7
فَإِذَا نُقِرَ فِي ٱلنَّاقُورِ
በቀንዱም በተነፋ ጊዜ (ነገሩ ይበረታል)፡፡
Surah Al-Muddathir, Verse 8
فَذَٰلِكَ يَوۡمَئِذٖ يَوۡمٌ عَسِيرٌ
ይህም (ጊዜ) ያ ቀን አስቸጋሪ ቀን ነው፡፡
Surah Al-Muddathir, Verse 9
عَلَى ٱلۡكَٰفِرِينَ غَيۡرُ يَسِيرٖ
በከሓዲዎች ላይ ገር ያልኾነ ነው፡፡
Surah Al-Muddathir, Verse 10
ذَرۡنِي وَمَنۡ خَلَقۡتُ وَحِيدٗا
አንድ ኾኖ ከፈጠርኩት ሰው ጋር ተዎኝ (እኔ እበቃሃለሁ)፡፡
Surah Al-Muddathir, Verse 11
وَجَعَلۡتُ لَهُۥ مَالٗا مَّمۡدُودٗا
ለእርሱም የተዘረጋን ገንዘብ (በያይነቱ) ያደረግሁለት፡፡
Surah Al-Muddathir, Verse 12
وَبَنِينَ شُهُودٗا
(በያደባባዩ) ተገኝዎች የኾኑ ወንዶች ልጆችንም፡፡
Surah Al-Muddathir, Verse 13
وَمَهَّدتُّ لَهُۥ تَمۡهِيدٗا
ለእርሱም (ኑሮውን) መዘርጋትን የዘረጋሁለት (ከኾነ ሰው ገር ተዎኝ)፡፡
Surah Al-Muddathir, Verse 14
ثُمَّ يَطۡمَعُ أَنۡ أَزِيدَ
ከዚያም ልጨምርለት ይከጅላል፡፡
Surah Al-Muddathir, Verse 15
كَلَّآۖ إِنَّهُۥ كَانَ لِأٓيَٰتِنَا عَنِيدٗا
ይከልከል፤ እርሱ ለአንቀጾቻችን በእርግጥ ተቃዋሚ ነበር፡፡
Surah Al-Muddathir, Verse 16
سَأُرۡهِقُهُۥ صَعُودًا
በእርግጥ ችግርን አስገድደዋለሁ፡፡
Surah Al-Muddathir, Verse 17
إِنَّهُۥ فَكَّرَ وَقَدَّرَ
እርሱ (በቁርኣን ነገር) ሐሰበ፤ ገመተም፡፡
Surah Al-Muddathir, Verse 18
فَقُتِلَ كَيۡفَ قَدَّرَ
ተረገመም፤ እንዴት ገመተ
Surah Al-Muddathir, Verse 19
ثُمَّ قُتِلَ كَيۡفَ قَدَّرَ
ከዚያም (ከሞት በኋላ) ተረገመ፡፡ እንዴት ገመተ
Surah Al-Muddathir, Verse 20
ثُمَّ نَظَرَ
ከዚያም እንደ ገና (በቁርኣኑ ነገር) ተመለከተ፡፡
Surah Al-Muddathir, Verse 21
ثُمَّ عَبَسَ وَبَسَرَ
ከዚያም ፊቱን አጨፈገገ፤ አኮማተረም፡፡
Surah Al-Muddathir, Verse 22
ثُمَّ أَدۡبَرَ وَٱسۡتَكۡبَرَ
ከዚያም (ከማመን) ዞረ፤ ኮራም፡፡
Surah Al-Muddathir, Verse 23
فَقَالَ إِنۡ هَٰذَآ إِلَّا سِحۡرٞ يُؤۡثَرُ
አለም «ይህ (ከሌላ) የሚቀዳ ድግምት እንጅ ሌላ አይደለም፡፡
Surah Al-Muddathir, Verse 24
إِنۡ هَٰذَآ إِلَّا قَوۡلُ ٱلۡبَشَرِ
«ይህ የሰው ቃል እንጅ ሌላ አይደለም፡፡»
Surah Al-Muddathir, Verse 25
سَأُصۡلِيهِ سَقَرَ
በሰቀር ውስጥ በእርግጥ አገባዋለሁ፡፡
Surah Al-Muddathir, Verse 26
وَمَآ أَدۡرَىٰكَ مَا سَقَرُ
ሰቀር ምን እንደኾነች ምን አሳወቀህ
Surah Al-Muddathir, Verse 27
لَا تُبۡقِي وَلَا تَذَرُ
(ያገኘችውን ሁሉ) አታስቀርም አትተውምም፡፡
Surah Al-Muddathir, Verse 28
لَوَّاحَةٞ لِّلۡبَشَرِ
ቆዳን በጣም አክሳይ ናት፡፡
Surah Al-Muddathir, Verse 29
عَلَيۡهَا تِسۡعَةَ عَشَرَ
በእርሷም ላይ አሥራ ዘጠኝ (ዘበኞች) አሉባት፡፡
Surah Al-Muddathir, Verse 30
وَمَا جَعَلۡنَآ أَصۡحَٰبَ ٱلنَّارِ إِلَّا مَلَـٰٓئِكَةٗۖ وَمَا جَعَلۡنَا عِدَّتَهُمۡ إِلَّا فِتۡنَةٗ لِّلَّذِينَ كَفَرُواْ لِيَسۡتَيۡقِنَ ٱلَّذِينَ أُوتُواْ ٱلۡكِتَٰبَ وَيَزۡدَادَ ٱلَّذِينَ ءَامَنُوٓاْ إِيمَٰنٗا وَلَا يَرۡتَابَ ٱلَّذِينَ أُوتُواْ ٱلۡكِتَٰبَ وَٱلۡمُؤۡمِنُونَ وَلِيَقُولَ ٱلَّذِينَ فِي قُلُوبِهِم مَّرَضٞ وَٱلۡكَٰفِرُونَ مَاذَآ أَرَادَ ٱللَّهُ بِهَٰذَا مَثَلٗاۚ كَذَٰلِكَ يُضِلُّ ٱللَّهُ مَن يَشَآءُ وَيَهۡدِي مَن يَشَآءُۚ وَمَا يَعۡلَمُ جُنُودَ رَبِّكَ إِلَّا هُوَۚ وَمَا هِيَ إِلَّا ذِكۡرَىٰ لِلۡبَشَرِ
የእሳትንም ዘበኞች መላእክት እንጅ ሌላ አላደረግንም፡፡ ቁጥራቸውንም ለእነዚያ ለካዱት መፈተኛ እንጅ አላደረግንም፡፡ እነዚያ መጽሐፍን የተሰጡት እንዲያረጋግጡ፣ እነዚያም ያመኑት እምነትን እንዲጨምሩ፣ እነዚያም መጽሐፍን የተሰጡትና ምእምናኖቹ እንዳይጠራጠሩ፣ እነዚያም በልቦቻቸው ውስጥ በሽታ ያለባቸው (መናፍቃን)፣ ከሓዲዎችም አላህ በዚህ (ቁጥር) ምን ምሳሌ ሽቷል? እንዲሉ (እንጅ አላደረግንም)፡፡ እንደዚሁ አላህ የሚሻውን ያጠምማል፡፡ የሚሻውንም ያቀናል፡፡ የጌታህንም ሰራዊት (ልክ) ከርሱ በቀር ማንም አያውቅም፡፡ እርሷም (የሰቀር እሳት) ለሰዎች መገሰጫ እንጅ ሌላ አይደለችም፡፡
Surah Al-Muddathir, Verse 31
كَلَّا وَٱلۡقَمَرِ
(ከክህደት) ይከልከሉ፡፡ በጨረቃ እምላለሁ፡፡
Surah Al-Muddathir, Verse 32
وَٱلَّيۡلِ إِذۡ أَدۡبَرَ
በሌሊቱም በኼደ ጊዜ፡፡
Surah Al-Muddathir, Verse 33
وَٱلصُّبۡحِ إِذَآ أَسۡفَرَ
በንጋቱም ባበራ ጊዜ፡፡
Surah Al-Muddathir, Verse 34
إِنَّهَا لَإِحۡدَى ٱلۡكُبَرِ
እርሷ (ሰቀር) ከታላላቆቹ (አደጋዎች) አንዷ ናት፡፡
Surah Al-Muddathir, Verse 35
نَذِيرٗا لِّلۡبَشَرِ
ለሰዎች አስፈራሪ ስትኾን፡፡
Surah Al-Muddathir, Verse 36
لِمَن شَآءَ مِنكُمۡ أَن يَتَقَدَّمَ أَوۡ يَتَأَخَّرَ
ከእናንተ (ወደ በጎ ነገር) መቅደምን ወይም ወደ ኋላ መቅረትን ለሻ ሰው (አስፈራሪ ስትኾኑ)፡፡
Surah Al-Muddathir, Verse 37
كُلُّ نَفۡسِۭ بِمَا كَسَبَتۡ رَهِينَةٌ
ነፍስ ሁሉ በሠራችው ሥራ ተያዥ ናት፡፡
Surah Al-Muddathir, Verse 38
إِلَّآ أَصۡحَٰبَ ٱلۡيَمِينِ
የቀኝ ባለቤቶች ብቻ ሲቀሩ፡፡
Surah Al-Muddathir, Verse 39
فِي جَنَّـٰتٖ يَتَسَآءَلُونَ
(እነርሱስ) በገነቶች ውስጥ ይጠያየቃሉ፡፡
Surah Al-Muddathir, Verse 40
عَنِ ٱلۡمُجۡرِمِينَ
ከአመጸኞቹ ኹነታ፡፡
Surah Al-Muddathir, Verse 41
مَا سَلَكَكُمۡ فِي سَقَرَ
(ይሏቸዋልም) «በሰቀር ውስጥ ምን አገባችሁ?»
Surah Al-Muddathir, Verse 42
قَالُواْ لَمۡ نَكُ مِنَ ٱلۡمُصَلِّينَ
(እነርሱም) ይላሉ «ከሰጋጆቹ አልነበርንም፡፡
Surah Al-Muddathir, Verse 43
وَلَمۡ نَكُ نُطۡعِمُ ٱلۡمِسۡكِينَ
«ለድኾችም የምናበላ አልነበርንም፡፡
Surah Al-Muddathir, Verse 44
وَكُنَّا نَخُوضُ مَعَ ٱلۡخَآئِضِينَ
«ከዘባራቂዎቹም ጋር እንዘባርቅ ነበርን፡፡
Surah Al-Muddathir, Verse 45
وَكُنَّا نُكَذِّبُ بِيَوۡمِ ٱلدِّينِ
«በፍርዱ ቀንም እናስተባብል ነበርን፡፡
Surah Al-Muddathir, Verse 46
حَتَّىٰٓ أَتَىٰنَا ٱلۡيَقِينُ
«እርግጠኛው (ሞት) እስከ መጣን ድረስ፡፡»
Surah Al-Muddathir, Verse 47
فَمَا تَنفَعُهُمۡ شَفَٰعَةُ ٱلشَّـٰفِعِينَ
የአማላጆችም ምልጃ አትጠቅማቸውም፡፡
Surah Al-Muddathir, Verse 48
فَمَا لَهُمۡ عَنِ ٱلتَّذۡكِرَةِ مُعۡرِضِينَ
ከግሣጼዬም (ከቁርኣን) የሚያፈገፍጉት ለእነርሱ ምን አልላቸው
Surah Al-Muddathir, Verse 49
كَأَنَّهُمۡ حُمُرٞ مُّسۡتَنفِرَةٞ
እነርሱ ልክ ደንባሪዎች የሜዳ አህዮች ይመስላሉ፡፡
Surah Al-Muddathir, Verse 50
فَرَّتۡ مِن قَسۡوَرَةِۭ
ከዐንበሳ የሸሹ፡፡
Surah Al-Muddathir, Verse 51
بَلۡ يُرِيدُ كُلُّ ٱمۡرِيٕٖ مِّنۡهُمۡ أَن يُؤۡتَىٰ صُحُفٗا مُّنَشَّرَةٗ
ይልቁንም ከእነርሱ እያንዳንዱ ሰው ሁሉ የተዘረጉ ጽሑፎችን እንዲስሰጥ ይፈልጋል፡፡
Surah Al-Muddathir, Verse 52
كَلَّاۖ بَل لَّا يَخَافُونَ ٱلۡأٓخِرَةَ
ይከልከሉ፡፡ ይልቁንም የመጨረሻይቱን ዓለም (ቅጣት) አይፈሩም፡፡
Surah Al-Muddathir, Verse 53
كَلَّآ إِنَّهُۥ تَذۡكِرَةٞ
ይከልከሉ፡፡ እርሱ (ቁርኣን) መገሠጫ ነው፡፡
Surah Al-Muddathir, Verse 54
فَمَن شَآءَ ذَكَرَهُۥ
ስለዚህ የሻ ሰው ይገሰጽበታል፡፡
Surah Al-Muddathir, Verse 55
وَمَا يَذۡكُرُونَ إِلَّآ أَن يَشَآءَ ٱللَّهُۚ هُوَ أَهۡلُ ٱلتَّقۡوَىٰ وَأَهۡلُ ٱلۡمَغۡفِرَةِ
አላህም ካልሻ በስተቀር አይገሠጹም፡፡ እርሱ (አላህ) የመፈራት ባለቤት የምሕረትም ባለቤት ነው፡፡
Surah Al-Muddathir, Verse 56