UAE Prayer Times

  • Dubai
  • Abu Dhabi
  • Sharjah
  • Ajman
  • Fujairah
  • Umm Al Quwain
  • Ras Al Khaimah
  • Quran Translations

Surah Al-Qiyama - Amharic Translation by Muhammed Sadiq And Muhammed Sani Habib


لَآ أُقۡسِمُ بِيَوۡمِ ٱلۡقِيَٰمَةِ

(ነገሩ ከሓዲዎች እንደሚሉት) አይደለም፡፡ በትንሣኤ ቀን እምላለሁ፡፡
Surah Al-Qiyama, Verse 1


وَلَآ أُقۡسِمُ بِٱلنَّفۡسِ ٱللَّوَّامَةِ

(ራሷን) ወቃሽ በኾነች ነፍስም እምላለሁ፡፡ (በእርግጥ ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡
Surah Al-Qiyama, Verse 2


أَيَحۡسَبُ ٱلۡإِنسَٰنُ أَلَّن نَّجۡمَعَ عِظَامَهُۥ

ሰው አጥንቶቹን አለመሰብሰባችንን ያስባልን
Surah Al-Qiyama, Verse 3


بَلَىٰ قَٰدِرِينَ عَلَىٰٓ أَن نُّسَوِّيَ بَنَانَهُۥ

አይደለም ጣቶቹን (ፊት እንደ ነበሩ) በማስተካከል ላይ ቻዮች ስንኾን (እንሰበስባቸዋለን)፡፡
Surah Al-Qiyama, Verse 4


بَلۡ يُرِيدُ ٱلۡإِنسَٰنُ لِيَفۡجُرَ أَمَامَهُۥ

ይልቁንም ሰው በፊቱ ባለው ነገር (በትንሣኤ) ሊያስተባብል ይፈልጋል፡፡
Surah Al-Qiyama, Verse 5


يَسۡـَٔلُ أَيَّانَ يَوۡمُ ٱلۡقِيَٰمَةِ

«የትንሣኤው ቀን መቼ ነው?» ሲል ይጠይቃል፡፡
Surah Al-Qiyama, Verse 6


فَإِذَا بَرِقَ ٱلۡبَصَرُ

ዓይንም በዋለለ ጊዜ፡፡
Surah Al-Qiyama, Verse 7


وَخَسَفَ ٱلۡقَمَرُ

ጨረቃም በጨለመ ጊዜ፡፡
Surah Al-Qiyama, Verse 8


وَجُمِعَ ٱلشَّمۡسُ وَٱلۡقَمَرُ

ፀሐይና ጨረቃም በተሰበሰቡ ጊዜ፡፡
Surah Al-Qiyama, Verse 9


يَقُولُ ٱلۡإِنسَٰنُ يَوۡمَئِذٍ أَيۡنَ ٱلۡمَفَرُّ

«ሰው በዚያ ቀን መሸሻው የት ነው?» ይላል፡፡
Surah Al-Qiyama, Verse 10


كَلَّا لَا وَزَرَ

ይከልከል፤ ምንም መጠጊያ የለም፡፡
Surah Al-Qiyama, Verse 11


إِلَىٰ رَبِّكَ يَوۡمَئِذٍ ٱلۡمُسۡتَقَرُّ

በዚያ ቀን መርጊያው ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡
Surah Al-Qiyama, Verse 12


يُنَبَّؤُاْ ٱلۡإِنسَٰنُ يَوۡمَئِذِۭ بِمَا قَدَّمَ وَأَخَّرَ

ሰው በዚያ ቀን ባስቀደመውና ባስቆየው ሁሉ ይነገራል፡፡
Surah Al-Qiyama, Verse 13


بَلِ ٱلۡإِنسَٰنُ عَلَىٰ نَفۡسِهِۦ بَصِيرَةٞ

በእርግጥም ሰው በነፍሱ ላይ አስረጅ ነው፡፡ (አካሎቹ ይመሰክሩበታል)፡፡
Surah Al-Qiyama, Verse 14


وَلَوۡ أَلۡقَىٰ مَعَاذِيرَهُۥ

ምክንያቶቹን ሁሉ ቢያመጣም እንኳ (አይሰማም)፡፡
Surah Al-Qiyama, Verse 15


لَا تُحَرِّكۡ بِهِۦ لِسَانَكَ لِتَعۡجَلَ بِهِۦٓ

በእርሱ (በቁርኣን ንባብ) ልትቸኩል ምላስህን በእርሱ አታላውስ፡፡
Surah Al-Qiyama, Verse 16


إِنَّ عَلَيۡنَا جَمۡعَهُۥ وَقُرۡءَانَهُۥ

(በልብህ ውስጥ) መሰብሰቡና ማንበቡ በእኛ ላይ ነውና፡፡
Surah Al-Qiyama, Verse 17


فَإِذَا قَرَأۡنَٰهُ فَٱتَّبِعۡ قُرۡءَانَهُۥ

ባነበብነውም ጊዜ (ካለቀ በኋላ) ንባቡን ተከተል፡፡
Surah Al-Qiyama, Verse 18


ثُمَّ إِنَّ عَلَيۡنَا بَيَانَهُۥ

ከዚያም ማብራራቱ በእኛ ላይ ነው፡፡
Surah Al-Qiyama, Verse 19


كَلَّا بَلۡ تُحِبُّونَ ٱلۡعَاجِلَةَ

(ከመጣደፍ) ተከልከል፡፡ ይልቁንም (ሰዎች) ፈጣኒቱን (ዓለም) ትወዳላችሁ፡፡
Surah Al-Qiyama, Verse 20


وَتَذَرُونَ ٱلۡأٓخِرَةَ

መጨረሻይቱንም (ዓለም) ትተዋላችሁ፡፡ (አትዘጋጁላትም)፡፡
Surah Al-Qiyama, Verse 21


وُجُوهٞ يَوۡمَئِذٖ نَّاضِرَةٌ

ፊቶች በዚያ ቀን አብሪዎች ናቸው፡፡
Surah Al-Qiyama, Verse 22


إِلَىٰ رَبِّهَا نَاظِرَةٞ

ወደ ጌታቸው ተመልካቾች ናቸው፡፡
Surah Al-Qiyama, Verse 23


وَوُجُوهٞ يَوۡمَئِذِۭ بَاسِرَةٞ

ፊቶችም በዚያ ቀን ጨፍጋጊዎች ናቸው፡፡
Surah Al-Qiyama, Verse 24


تَظُنُّ أَن يُفۡعَلَ بِهَا فَاقِرَةٞ

በርሳቸውም ዐደጋ እንደሚሠራባቸው ያረጋግጣሉ፡፡
Surah Al-Qiyama, Verse 25


كَلَّآ إِذَا بَلَغَتِ ٱلتَّرَاقِيَ

ንቁ (ነፍስ) ብሪዎችን በደረሰች ጊዜ፤
Surah Al-Qiyama, Verse 26


وَقِيلَ مَنۡۜ رَاقٖ

«አሻሪው ማነው?» በተባለም ጊዜ፡፡
Surah Al-Qiyama, Verse 27


وَظَنَّ أَنَّهُ ٱلۡفِرَاقُ

(ሕመምተኛው) እርሱ (የሰፈረበት ነገር ከዚህ ዓለም) መልለየት መኾኑን ባረጋገጠም ጊዜ፡፡
Surah Al-Qiyama, Verse 28


وَٱلۡتَفَّتِ ٱلسَّاقُ بِٱلسَّاقِ

ባትም በባት በተጣበቀች ጊዜ፡፡
Surah Al-Qiyama, Verse 29


إِلَىٰ رَبِّكَ يَوۡمَئِذٍ ٱلۡمَسَاقُ

በዚያ ቀን መነዳቱ ወደ ጌታህ (ፍርድ) ነው፡፡
Surah Al-Qiyama, Verse 30


فَلَا صَدَّقَ وَلَا صَلَّىٰ

አላመነምም አልሰገደምም፡፡
Surah Al-Qiyama, Verse 31


وَلَٰكِن كَذَّبَ وَتَوَلَّىٰ

ግን አስተባበለ፤ (ከእምነት) ዞረም፡፡
Surah Al-Qiyama, Verse 32


ثُمَّ ذَهَبَ إِلَىٰٓ أَهۡلِهِۦ يَتَمَطَّىٰٓ

ከዚያም እየተንጎባለለ ወደ ቤተሰቡ ኼደ፡፡
Surah Al-Qiyama, Verse 33


أَوۡلَىٰ لَكَ فَأَوۡلَىٰ

የምትጠላውን ነገር (አላህ) ያስከትልህ፡፡ ለአንተ ተገቢህም ነው፡፡
Surah Al-Qiyama, Verse 34


ثُمَّ أَوۡلَىٰ لَكَ فَأَوۡلَىٰٓ

ከዚያም ጥፋት ይጠጋህ ለአንተ የተገባህም ነው፡፡
Surah Al-Qiyama, Verse 35


أَيَحۡسَبُ ٱلۡإِنسَٰنُ أَن يُتۡرَكَ سُدًى

ሰው ስድ ኾኖ መትተውን ይጠረጥራልን
Surah Al-Qiyama, Verse 36


أَلَمۡ يَكُ نُطۡفَةٗ مِّن مَّنِيّٖ يُمۡنَىٰ

የሚፈሰስ ከኾነ የፍትወት ጠብታ አልነበረምን
Surah Al-Qiyama, Verse 37


ثُمَّ كَانَ عَلَقَةٗ فَخَلَقَ فَسَوَّىٰ

ከዚያም የረጋ ደም ኾነ (አላህ ሰው አድርጎ) ፈጠረውም፡፡ አስተካከለውም፡፡
Surah Al-Qiyama, Verse 38


فَجَعَلَ مِنۡهُ ٱلزَّوۡجَيۡنِ ٱلذَّكَرَ وَٱلۡأُنثَىٰٓ

ከእርሱም ሁለት ዓይነቶችን ወንድና ሴትን አደረገ፡፡
Surah Al-Qiyama, Verse 39


أَلَيۡسَ ذَٰلِكَ بِقَٰدِرٍ عَلَىٰٓ أَن يُحۡـِۧيَ ٱلۡمَوۡتَىٰ

ይህ (ጌታ) ሙታንን ሕያው በማድረግ ላይ ቻይ አይደለምን
Surah Al-Qiyama, Verse 40


Author: Muhammed Sadiq And Muhammed Sani Habib


<< Surah 74
>> Surah 76

Amharic Translations by other Authors


Amharic Translation By Muhammed Sadiq And Muhammed Sani Habib
Amharic Translation By Muhammed Sadiq And Muhammed Sani Habib
Amharic Translation By Muhammed Sadiq And Muhammed Sani Habib
Popular Areas
Apartments for rent in Dubai Apartments for rent Abu Dhabi Villas for rent in Dubai House for rent Abu Dhabi Apartments for sale in Dubai Apartments for sale in Abu Dhabi Flat for rent Sharjah
Popular Searches
Studios for rent in UAE Apartments for rent in UAE Villas for rent in UAE Apartments for sale in UAE Villas for sale in UAE Land for sale in UAE Dubai Real Estate
Trending Areas
Apartments for rent in Dubai Marina Apartments for sale in Dubai Marina Villa for rent in Sharjah Villa for sale in Dubai Flat for rent in Ajman Studio for rent in Abu Dhabi Villa for rent in Ajman
Trending Searches
Villa for rent in Abu Dhabi Shop for rent in Dubai Villas for sale in Ajman Studio for rent in Sharjah 1 Bedroom Apartment for rent in Dubai Property for rent in Abu Dhabi Commercial properties for sale
© Copyright Dubai Prayer Time. All Rights Reserved
Designed by Prayer Time In Dubai