Surah An-Naba - Amharic Translation by Muhammed Sadiq And Muhammed Sani Habib
عَمَّ يَتَسَآءَلُونَ
ከምን ነገር ይጠያየቃሉ
Surah An-Naba, Verse 1
عَنِ ٱلنَّبَإِ ٱلۡعَظِيمِ
ከታላቁ ዜና (ከቁርኣን ይጠያየቃሉ)፡፡
Surah An-Naba, Verse 2
ٱلَّذِي هُمۡ فِيهِ مُخۡتَلِفُونَ
ከዚያ እነርሱ በእርሱ የተለያዩበት ከኾነው፡፡
Surah An-Naba, Verse 3
كَلَّا سَيَعۡلَمُونَ
ይከልከሉ፤ ወደፊት (የሚደርስበቸውን) በእርግጥ ያውቃሉ፡፡
Surah An-Naba, Verse 4
ثُمَّ كَلَّا سَيَعۡلَمُونَ
ከዚያም ይከልከሉ፤ ወደፊት ያውቃሉ፡፡
Surah An-Naba, Verse 5
أَلَمۡ نَجۡعَلِ ٱلۡأَرۡضَ مِهَٰدٗا
ምድርን ምንጣፍ አላደረግንምን
Surah An-Naba, Verse 6
وَٱلۡجِبَالَ أَوۡتَادٗا
ጋራዎችንም ችካሎች አላደረግንምን
Surah An-Naba, Verse 7
وَخَلَقۡنَٰكُمۡ أَزۡوَٰجٗا
ብዙ ዓይነቶችም አድርገን ፈጠርናችሁ፡፡
Surah An-Naba, Verse 8
وَجَعَلۡنَا نَوۡمَكُمۡ سُبَاتٗا
እንቅልፋችሁንም ዕረፍት አደረግን፡፡
Surah An-Naba, Verse 9
وَجَعَلۡنَا ٱلَّيۡلَ لِبَاسٗا
ሌሊቱንም ልባስ አደረግን፡፡
Surah An-Naba, Verse 10
وَجَعَلۡنَا ٱلنَّهَارَ مَعَاشٗا
ቀኑንም (ለኑሮ) መስሪያ አደረግን፡፡
Surah An-Naba, Verse 11
وَبَنَيۡنَا فَوۡقَكُمۡ سَبۡعٗا شِدَادٗا
ከበላያችሁም ሰባትን ብርቱዎች (ሰማያት) ገነባን፡፡
Surah An-Naba, Verse 12
وَجَعَلۡنَا سِرَاجٗا وَهَّاجٗا
አንጸባራቂ ብርሃንንም አደረግን፡፡
Surah An-Naba, Verse 13
وَأَنزَلۡنَا مِنَ ٱلۡمُعۡصِرَٰتِ مَآءٗ ثَجَّاجٗا
ከአረገዙት ደመናዎችም ተንቧቢ ውሃን አወረድን፡፡
Surah An-Naba, Verse 14
لِّنُخۡرِجَ بِهِۦ حَبّٗا وَنَبَاتٗا
በእርሱ እኽልንና ቅጠላ ቅጠልን እናወጣ ዘንድ (አወረድን)፡፡
Surah An-Naba, Verse 15
وَجَنَّـٰتٍ أَلۡفَافًا
የተቆላለፉ አትክልቶችንም፡፡
Surah An-Naba, Verse 16
إِنَّ يَوۡمَ ٱلۡفَصۡلِ كَانَ مِيقَٰتٗا
የመለያው ቀን የተወሰነ ጊዜ ነው፡፡
Surah An-Naba, Verse 17
يَوۡمَ يُنفَخُ فِي ٱلصُّورِ فَتَأۡتُونَ أَفۡوَاجٗا
በቀንዱ በሚነፋና የተለያዩ ጭፍሮች ኾናችሁ በምትመጡ ቀን ነው፡፡
Surah An-Naba, Verse 18
وَفُتِحَتِ ٱلسَّمَآءُ فَكَانَتۡ أَبۡوَٰبٗا
ሰማይም በምትከፈትና (ባለ) ደጃፎችም በምትኾንበት፡፡
Surah An-Naba, Verse 19
وَسُيِّرَتِ ٱلۡجِبَالُ فَكَانَتۡ سَرَابًا
ጋራዎችም በሚነዱበት (እንደ) ሲሪብዱም በሚኾኑበት (ቀን) ነው፡፡
Surah An-Naba, Verse 20
إِنَّ جَهَنَّمَ كَانَتۡ مِرۡصَادٗا
ገሀነም መጠባበቂያ (ስፍራ) ናት፡፡
Surah An-Naba, Verse 21
لِّلطَّـٰغِينَ مَـَٔابٗا
ለሕግ ተላላፊዎች መመለሻ ስትኾን፡፡
Surah An-Naba, Verse 22
لَّـٰبِثِينَ فِيهَآ أَحۡقَابٗا
በውስጧ ብዙን ዘመናት ነዋሪዎች ሲኾኑ፤
Surah An-Naba, Verse 23
لَّا يَذُوقُونَ فِيهَا بَرۡدٗا وَلَا شَرَابًا
በውስጧ ቅዝቃዜንም መጠጥንም አይቀምሱም፡፡
Surah An-Naba, Verse 24
إِلَّا حَمِيمٗا وَغَسَّاقٗا
ግን ሙቅ ውሃንና እዥን (ይቀምሳሉ)፡፡
Surah An-Naba, Verse 25
جَزَآءٗ وِفَاقًا
ተስማሚን ምንዳ ይምመነዳሉ፡፡
Surah An-Naba, Verse 26
إِنَّهُمۡ كَانُواْ لَا يَرۡجُونَ حِسَابٗا
እነርሱ ምርመራን የማይፈሩ ነበሩና፡፡
Surah An-Naba, Verse 27
وَكَذَّبُواْ بِـَٔايَٰتِنَا كِذَّابٗا
በአንቀጾቻችንም ማስተባበልን አስተባበሉና፡፡
Surah An-Naba, Verse 28
وَكُلَّ شَيۡءٍ أَحۡصَيۡنَٰهُ كِتَٰبٗا
ነገሩንም ሁሉ የተጻፈ ሲኾን አጠቃለልነው፡፡
Surah An-Naba, Verse 29
فَذُوقُواْ فَلَن نَّزِيدَكُمۡ إِلَّا عَذَابًا
ቅመሱም ቅጣትንም እንጅ (ሌላን) አንጨምራችሁም (ይባላሉ)፡፡
Surah An-Naba, Verse 30
إِنَّ لِلۡمُتَّقِينَ مَفَازًا
ለጥንቁቆቹ መዳኛ ስፍራ አልላቸው፡፡
Surah An-Naba, Verse 31
حَدَآئِقَ وَأَعۡنَٰبٗا
አትክልቶችና ወይኖችም፡፡
Surah An-Naba, Verse 32
وَكَوَاعِبَ أَتۡرَابٗا
እኩያዎች የኾኑ ጡተ ጉቻማዎችም፡፡
Surah An-Naba, Verse 33
وَكَأۡسٗا دِهَاقٗا
የተሞሉ ብርጭቆዎችም፡፡
Surah An-Naba, Verse 34
لَّا يَسۡمَعُونَ فِيهَا لَغۡوٗا وَلَا كِذَّـٰبٗا
በውስጧ ትርፍ ቃልንም ማስዋሸትንም አይሰሙም፡፡
Surah An-Naba, Verse 35
جَزَآءٗ مِّن رَّبِّكَ عَطَآءً حِسَابٗا
ከጌታህ የኾነን ምንዳ በቂ ስጦታን (ተሰጡ)፡፡
Surah An-Naba, Verse 36
رَّبِّ ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلۡأَرۡضِ وَمَا بَيۡنَهُمَا ٱلرَّحۡمَٰنِۖ لَا يَمۡلِكُونَ مِنۡهُ خِطَابٗا
የሰማያትና የምድር በመካከላቸውም ያለው ሁሉ ጌታ በጣም አዛኝ ከኾነው (ተመነዱ)፡፡ ከእርሱ ጋር መነጋገርን አይችሉም፡፡
Surah An-Naba, Verse 37
يَوۡمَ يَقُومُ ٱلرُّوحُ وَٱلۡمَلَـٰٓئِكَةُ صَفّٗاۖ لَّا يَتَكَلَّمُونَ إِلَّا مَنۡ أَذِنَ لَهُ ٱلرَّحۡمَٰنُ وَقَالَ صَوَابٗا
መንፈሱ (ጂብሪል) መላእክቶቹም የተሰለፉ ኾነው በሚቆሙ ቀን አል-ረሕማን ለእርሱ የፈቀደለትና ትክክለኛን ቃል ያለ ሰው ቢኾን እንጅ (መነጋገርን አይችሉም)፡፡
Surah An-Naba, Verse 38
ذَٰلِكَ ٱلۡيَوۡمُ ٱلۡحَقُّۖ فَمَن شَآءَ ٱتَّخَذَ إِلَىٰ رَبِّهِۦ مَـَٔابًا
ይህ የተረጋገጠው ቀን ነው፡፡ የሻም ሰው ወደ ጌታው መመለስን ይይዛል፡፡
Surah An-Naba, Verse 39
إِنَّآ أَنذَرۡنَٰكُمۡ عَذَابٗا قَرِيبٗا يَوۡمَ يَنظُرُ ٱلۡمَرۡءُ مَا قَدَّمَتۡ يَدَاهُ وَيَقُولُ ٱلۡكَافِرُ يَٰلَيۡتَنِي كُنتُ تُرَٰبَۢا
እኛ ሰው ሁሉ እጆቹ ያስቀደሙትን በሚያይበትና ከሓዲውም ዋ ምኞቴ! ምንነው ዐፈር በኾንኩ በሚልበት ቀን ቅርብ የኾነን ቅጣት አስጠነቀቅናችሁ፡፡
Surah An-Naba, Verse 40