Surah An-Naziat - Amharic Translation by Muhammed Sadiq And Muhammed Sani Habib
وَٱلنَّـٰزِعَٰتِ غَرۡقٗا
በኃይል አውጪዎች በኾኑት፤
Surah An-Naziat, Verse 1
وَٱلنَّـٰشِطَٰتِ نَشۡطٗا
በቀስታ መምዘዝንም መዘዦች በኾኑት፤
Surah An-Naziat, Verse 2
وَٱلسَّـٰبِحَٰتِ سَبۡحٗا
መዋኘትም ዋኚዎች በኾኑት፤
Surah An-Naziat, Verse 3
فَٱلسَّـٰبِقَٰتِ سَبۡقٗا
መቅደምንም ቀዳሚዎች በኾኑት፤
Surah An-Naziat, Verse 4
فَٱلۡمُدَبِّرَٰتِ أَمۡرٗا
ነገርንም አስተናባሪዎች በኾኑት (መላእክት) እምላለሁ፡፡ (በእርግጥ ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡
Surah An-Naziat, Verse 5
يَوۡمَ تَرۡجُفُ ٱلرَّاجِفَةُ
ተርገፍጋፊይቱ (ምድር) በምትርገፈገፍበት ቀን፤
Surah An-Naziat, Verse 6
تَتۡبَعُهَا ٱلرَّادِفَةُ
ለጣቂይቱ የምትከተላት ስትኾን (ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡
Surah An-Naziat, Verse 7
قُلُوبٞ يَوۡمَئِذٖ وَاجِفَةٌ
በዚያ ቀን ልቦች ተሸባሪዎች ናቸው፡፡
Surah An-Naziat, Verse 8
أَبۡصَٰرُهَا خَٰشِعَةٞ
ዓይኖቻቸው ተዋራጆች (አቀርቃሪዎች) ናቸው፡፡
Surah An-Naziat, Verse 9
يَقُولُونَ أَءِنَّا لَمَرۡدُودُونَ فِي ٱلۡحَافِرَةِ
«እኛ ወደ መጀመሪያይቱ ኹነታ ተመላሾች ነን?» ይላሉ፡፡
Surah An-Naziat, Verse 10
أَءِذَا كُنَّا عِظَٰمٗا نَّخِرَةٗ
«የበሰበሱ አጥንቶች በኾን ጊዜ (እንቀሰቀሳለን?)»
Surah An-Naziat, Verse 11
قَالُواْ تِلۡكَ إِذٗا كَرَّةٌ خَاسِرَةٞ
«ይህቺ ያን ጊዜ ባለ ከሳራ መመለስ ናት» ይላሉ፡፡
Surah An-Naziat, Verse 12
فَإِنَّمَا هِيَ زَجۡرَةٞ وَٰحِدَةٞ
እርሷም አንዲት ጩኸት ብቻ ናት፡፡
Surah An-Naziat, Verse 13
فَإِذَا هُم بِٱلسَّاهِرَةِ
ወዲያውኑም እነርሱ እንቅልፍ በሌለባት (ምድር) ላይ ይኾናሉ፡፡
Surah An-Naziat, Verse 14
هَلۡ أَتَىٰكَ حَدِيثُ مُوسَىٰٓ
የሙሳ ወሬ መጣልህን
Surah An-Naziat, Verse 15
إِذۡ نَادَىٰهُ رَبُّهُۥ بِٱلۡوَادِ ٱلۡمُقَدَّسِ طُوًى
ጌታው በተቀደሰው ሸለቆ በጡዋ በጠራው ጊዜ፤
Surah An-Naziat, Verse 16
ٱذۡهَبۡ إِلَىٰ فِرۡعَوۡنَ إِنَّهُۥ طَغَىٰ
ወደ ፈርዖን ኺድ፡፡ እርሱ ወሰን አልፏልና፡፡
Surah An-Naziat, Verse 17
فَقُلۡ هَل لَّكَ إِلَىٰٓ أَن تَزَكَّىٰ
በለውም፡- «ወደ መጥራራትህ ላንተ (መንገድ) አለህን?»
Surah An-Naziat, Verse 18
وَأَهۡدِيَكَ إِلَىٰ رَبِّكَ فَتَخۡشَىٰ
«ወደ ጌታህም ልመራህ ትፈራውም ዘንድ፤ (መንገድ አለህን?)» አለው፡፡
Surah An-Naziat, Verse 19
فَأَرَىٰهُ ٱلۡأٓيَةَ ٱلۡكُبۡرَىٰ
ታላቂቱንም ተዓምር አሳየው፡፡
Surah An-Naziat, Verse 20
فَكَذَّبَ وَعَصَىٰ
አስተባበለም፤ አመጸም፡፡
Surah An-Naziat, Verse 21
ثُمَّ أَدۡبَرَ يَسۡعَىٰ
ከዚያም (ለማጥፋት) የሚተጋ ኾኖ ዞረ፡፡
Surah An-Naziat, Verse 22
فَحَشَرَ فَنَادَىٰ
(ሰራዊቶቹን) ሰበሰበም፤ ተጣራም፡፡
Surah An-Naziat, Verse 23
فَقَالَ أَنَا۠ رَبُّكُمُ ٱلۡأَعۡلَىٰ
አለም፡- «እኔ ታላቁ ጌታችሁ ነኝ፡፡»
Surah An-Naziat, Verse 24
فَأَخَذَهُ ٱللَّهُ نَكَالَ ٱلۡأٓخِرَةِ وَٱلۡأُولَىٰٓ
አላህም በኋለኛይቱና በፊተኛይቱ (ቃል) ቅጣት ያዘው፡፡
Surah An-Naziat, Verse 25
إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَعِبۡرَةٗ لِّمَن يَخۡشَىٰٓ
በዚህ ውስጥ ለሚፈራ ሰው በእርግጥ መገምገሚያ አለበት፡፡
Surah An-Naziat, Verse 26
ءَأَنتُمۡ أَشَدُّ خَلۡقًا أَمِ ٱلسَّمَآءُۚ بَنَىٰهَا
ባፈጣጠር እናንተ ይበልጥ የበረታችሁ ናችሁን? ወይንስ ሰማይ? (አላህ) ገነባት፡፡
Surah An-Naziat, Verse 27
رَفَعَ سَمۡكَهَا فَسَوَّىٰهَا
ከፍታዋን አጓነ፤ አስተካከላትም፡፡
Surah An-Naziat, Verse 28
وَأَغۡطَشَ لَيۡلَهَا وَأَخۡرَجَ ضُحَىٰهَا
ሌሊቷንም አጨለመ፡፡ ቀንዋንም ገለጸ፡፡
Surah An-Naziat, Verse 29
وَٱلۡأَرۡضَ بَعۡدَ ذَٰلِكَ دَحَىٰهَآ
ምድርንም ከዚህ በኋላ ዘረጋት፡፡
Surah An-Naziat, Verse 30
أَخۡرَجَ مِنۡهَا مَآءَهَا وَمَرۡعَىٰهَا
ውሃዋንና ግጦሿን ከእርሷ አወጣ፡፡
Surah An-Naziat, Verse 31
وَٱلۡجِبَالَ أَرۡسَىٰهَا
ጋራዎችንም አደላደላቸው፡፡
Surah An-Naziat, Verse 32
مَتَٰعٗا لَّكُمۡ وَلِأَنۡعَٰمِكُمۡ
ለእናንተና ለእንስሶቻችሁ መጣቀሚያ ይኾን ዘንድ (ይህን አደረገ)፡፡
Surah An-Naziat, Verse 33
فَإِذَا جَآءَتِ ٱلطَّآمَّةُ ٱلۡكُبۡرَىٰ
ታላቂቱም መዐት በመጣች ጊዜ፣
Surah An-Naziat, Verse 34
يَوۡمَ يَتَذَكَّرُ ٱلۡإِنسَٰنُ مَا سَعَىٰ
ሰው ሁሉ የሠራውን በሚያስታውስበት ቀን፣
Surah An-Naziat, Verse 35
وَبُرِّزَتِ ٱلۡجَحِيمُ لِمَن يَرَىٰ
ገሀነምም ለሚያይ ሰው በተገለጠች ጊዜ፣
Surah An-Naziat, Verse 36
فَأَمَّا مَن طَغَىٰ
የካደ ሰውማ፣
Surah An-Naziat, Verse 37
وَءَاثَرَ ٱلۡحَيَوٰةَ ٱلدُّنۡيَا
ቅርቢቱንም ሕይወት የመረጠ፣
Surah An-Naziat, Verse 38
فَإِنَّ ٱلۡجَحِيمَ هِيَ ٱلۡمَأۡوَىٰ
ገሀነም እርሷ በእርግጥ መኖሪያው ናት፡፡
Surah An-Naziat, Verse 39
وَأَمَّا مَنۡ خَافَ مَقَامَ رَبِّهِۦ وَنَهَى ٱلنَّفۡسَ عَنِ ٱلۡهَوَىٰ
በጌታው ፊት መቆምን የፈራ ሰውማ ነፍሱንም ከዝንባሌዋ የከለከለ
Surah An-Naziat, Verse 40
فَإِنَّ ٱلۡجَنَّةَ هِيَ ٱلۡمَأۡوَىٰ
ገነት እርሷ በእርግጥ መኖሪያው ናት፡፡
Surah An-Naziat, Verse 41
يَسۡـَٔلُونَكَ عَنِ ٱلسَّاعَةِ أَيَّانَ مُرۡسَىٰهَا
«ከሰዓቲቱ መቼ ነው መኾኛዋ?» ሲሉ ይጠይቁሃል፡፡
Surah An-Naziat, Verse 42
فِيمَ أَنتَ مِن ذِكۡرَىٰهَآ
አንተ እርሷን ከማስታወስ በምን ውስጥ ነህ
Surah An-Naziat, Verse 43
إِلَىٰ رَبِّكَ مُنتَهَىٰهَآ
(የዕውቀት) መጨረሻዋ ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡
Surah An-Naziat, Verse 44
إِنَّمَآ أَنتَ مُنذِرُ مَن يَخۡشَىٰهَا
አንተ የሚፈራትን ሰው አስፈራሪ ብቻ ነህ፡፡
Surah An-Naziat, Verse 45
كَأَنَّهُمۡ يَوۡمَ يَرَوۡنَهَا لَمۡ يَلۡبَثُوٓاْ إِلَّا عَشِيَّةً أَوۡ ضُحَىٰهَا
እነርሱ በሚያዩዋት ቀን ያንዲት ቀን ምሽትን ወይም ረፏዷን እንጅ ያልቆዩ ይመስላሉ፡፡
Surah An-Naziat, Verse 46